am_tn/gen/31/29.md

1.2 KiB

እናንተን ልጐዳችሁ ነበር

እዚህ “እናንተ” ብዙና ከያዕቆብ ጋር ያሉትን ሁሉ ያመለክታል:: አት: “ሊጐዳችሁ የሚያስችለኝ ከእኔ ጋር ብዙ ሰዎች ነበሩ” (የሁለተኛ ሰው አገላለጽ ይመልከቱ)

ያዕቆብን ክፉም ሆነ ደግ እንዳትናገረው ተጠንቀቅ አለኝ

“ክፉ ሆነ ደግ” የሚለው ሀረግ የተጠቀመው “ምንም” ለማለት ነው፡፡ በዘፍጥረት 31:24 ይህን እንዴት እንደተረጐሙ ይመልከቱ:: አት፡ “ያዕቆብን ከመሄድ ለማቋረጥ ለመሞከር ምንም ነገር እንዳትናገር” (See: Merism)

አንተም ሄደሃል

አንተ የሚለው ነጠላና ያዕቆብን ያመለክታል:: (የሁለተኛ ሰው አገላለጽ ይመልከቱ)

ወደ አባትህም ቤት

እዚህ ቤት ቤተሰብን ይወክላል:: አት: “ወደ አባትህና ሌሎች ቤተሰብህ ቤት ለመመለስ” (ክፍልን ሙሉና ሙሉውን ክፍል አድርጐ የመግለጽ ዘይቤ ይመልከቱ)

አምላኮቼን

ጣዖቶቼን