am_tn/gen/30/01.md

1.1 KiB

ራሔል ለያዕቆብ ልጅን እንዳልወለደች ባየች ጊዜ

ራሔል ማርገዝ እንዳልቻለች ባወቀች ጊዜ

እሞታለሁ

ራሔል ልጅ ባለመኖርዋ ምነኛ እንደተከፋች ማጋነንዋ ነው:: አት: ምንም እንደማልጠቅም ይሰማኛል:: (በማጋነንና በገሃድ የመግለጽ ዘይቤ ይመልከቱ)

ልጅ ስጠኝ

እንዳረግዝ አድርገኝ

ያዕቆብም ቁጣ በራሔል ላይ ነደደ

የያዕቆብ ቁጣ እንደ እሳት ተደርጐ ተገልጾአል፡፡ አት፡ “ያዕቆብ ራሔልን በጣም ተቆጣት” (ዘይቤያዊ አነጋገር ይመልከቱ)

እኔ እንዳትወልጂ ያደረግሽን እግዚአብሔርን መሰልኩሽን?

ይህ ያዕቆብ ራሔልን ለመቆጣት የተጠቀመው ቅኔያዊ ጥያቄ ነው:: ይህም እንደ ዐረፍተ ነገር ልተረጐም ይችላል፡፡ አት፡ “እኔ እግዚአብሔር አይደለሁም! ልጅ እንዳትወልጂ የሚከለክለው እኔ አይደለሁም” (ቅኔ አዘል ጥያቄዎችን ይመልከቱ)