am_tn/exo/39/36.md

811 B

አጠቃላይ ምልከታ፦

በባስልኤልና በሥሩ ያሉ የሥራ ቡድኖች ማደሪያውንና መገናኛ ድንኳኑን ለሙሴ ሲያቀርቡ እናያለን።

• የገጹንም ኅብስት

ህልዎተ እግዚአብሔር መገለጫ የሆነው ዳቦ ነው። በመገናኛው ድንኳን ወይም በማደሪያው ውስጥ የእግዚአብሔር መኖር ምልክት የሆነው ዳቦ ነው። ከተራ ዳቦ የተለየ መሆኑን ለማመልከት በአማርኛ ኅብስት ተብሏል። ዘጸአት 25፡30 ተመልከት

• ከናስ መጫሪያው

እንጨት በእሳት ሲነድ በአንድ በኩል እንጨቱን ለመያዝ የሚያገለግል ከነሐስ ብረት የተሰራ ዘንግ ማለት ነው።