811 B
811 B
አጠቃላይ ምልከታ፦
በባስልኤልና በሥሩ ያሉ የሥራ ቡድኖች ማደሪያውንና መገናኛ ድንኳኑን ለሙሴ ሲያቀርቡ እናያለን።
• የገጹንም ኅብስት
ህልዎተ እግዚአብሔር መገለጫ የሆነው ዳቦ ነው። በመገናኛው ድንኳን ወይም በማደሪያው ውስጥ የእግዚአብሔር መኖር ምልክት የሆነው ዳቦ ነው። ከተራ ዳቦ የተለየ መሆኑን ለማመልከት በአማርኛ ኅብስት ተብሏል። ዘጸአት 25፡30 ተመልከት
• ከናስ መጫሪያው
እንጨት በእሳት ሲነድ በአንድ በኩል እንጨቱን ለመያዝ የሚያገለግል ከነሐስ ብረት የተሰራ ዘንግ ማለት ነው።