am_tn/exo/39/08.md

1.1 KiB

አጠቃላይ ምልከታ፦

በመገናኛው ድንኳን የሚያገለግሉ ካህናት ልብሶች ዝግጅት ይቀጥላል

• አደረገው

አዲሱ አማርኛ እና መደበኛው አማርኛው ትርጉም “ሠሩት” ብሎ በወል ስም ይጠቅሳሉ። የዕብራይስጡ ቅጅ፥ የቀድሞ አማርኛ ቅጅና ለሎች ተአማኒነት ያላቸው ቅጅዎች “አደረገው” ይላሉ። “ሠሩት” በሚል የተረጎሙት ትኩረታቸው ባስልኤል፥ ኤልያብና ሌሎች ሰዎችን ታሳቢ በማድረግ ነው። “አደረገው” በሚል የተረጎሙት ትኩረታቸው የሥራው ዋና መሪ ባስልኤል ስለሆነ ትኩረታቸው በእርሱ ላይ ነው። የዕብራይስጡ ቅጅ ትኩረቱ በባስልኤል ላይ ስለሆነ “እርሱ አደረገው” የሚል ነው። ስለሆነም አደረገው የሚለው ትክክለኛ ትርጉም ነው።

• አንድ ስንዝር

በዘመናዊ የርቀት መለኪያ ከ20-22 ሴንቲ ሜትር ያህል ነው።