am_tn/exo/34/19.md

1.4 KiB

አጠቃላይ ምልከታ፦

እግዚአብሔር (ያህዌ) እስራኤላውያን ምን ማድረግ እንዳለባቸው በሙሴ በኩል ያሳስባቸዋል።

• ማኅፀንንም የሚከፍት (ዘይቤያዊ አነጋገር)

በኩር ሆኖ የሚወለድ ወይም የሚወጣ

• ትዋጀዋለህ

በኩር ሆኖ የሚወለድ ወንድ እና አህያ የእግዚአብሔር (የያህዌ) ነው፤ ነገር ግን መስዋእት ሆነው እንዲቀርቡለት ያህዌ አይፈልግም። በእነርሱ ፋንታ እስራኤላውያን በጎችን እንዲሰዉለት ተጠይቀዋል። ስለሆነም እስራኤላውያን በኩር ሆኖ የተወለደን አህያ ወይም ወንድ ልጅ ከእግዚአብሔር መልሰው እንዲገዙ ተፈቅዶላቸዋል። የምይዋጁ ከሆነ አንገቱን ቆልምመው ለመስዋዕት እንዳይቀርብ እንድያደርጉ ተጠይቀዋል።

• በፊቴም አንድ ሰው ባዶ እጁን አይታይ

ይህ አነጋገር እግዚአብሔር ማንም ሰው ወደ ፊቱ ሲመጣ የሆነ ነገር ተሸክሞ እንድመጣ የሚጠይቅ ይመስላል። ነገር ግን ይህ ወካይ ዘይቤ የሚያሳየው ወደ እኔ የሚመጣ ማንም ቢሆን መስዋዕት ሳይዝ አይምጣ ወይም ወደ እኔ የሚመጣ ማንም ቢሆን መስዋዕት ማምጣት አለበት