am_tn/exo/33/17.md

1.1 KiB

አጠቃላይ ምልከታ፦

እግዚአብሔር “አንተ’ እያለ በነጠላ ቁጥር የሚናገረው “ሙሴን” የሚመለከት ነው።

• በፊቴ ሞገስ ስላገኘህ

በዚህ ሀረግ “ሞገስ ስላገኘህ” የሚለው የሚያመለክተው ዘይቤያዊ አነጋገር ሲሆን ዕውቅና ያገኘ ወይም እግዚአብሔር (ያህዌ) በሙሴ ደስ ተሰኘ ማለት ነው። “በፊቴ” የተባለው በእግዚአብሔር እይታ ወይም የእግዚአብሔርን ግምገማ የሚመለከት ነው። አማራጭ ትርጉም፦ እኔ አንተን ገምግሜ ዕውቅና ሰጥቼሃለሁ ወይም በአንተ ተደስቻለሁ/በአንተ ደስ ይለኛል/

• በስምህም ስላወቅሁህ (ዘይቤያዊ ንግግር)

አንድን ሰው በስም ማወቅ ያንን ሰው በሚገባ ወይም በትክክል እንደማወቅ ነው። አማራጭ ትርጉም፦ እኔ አንተን በደንብ ወይም በሚገባ አውቅሃለሁ