am_tn/exo/32/33.md

1.4 KiB

• እርሱን ከመጽሐፌ እደመስሰዋለሁ

“እርሱን” የሚለው ያንን ሀጢአት የሰራውን ሰው ስም ማለት ነው። አማራጭ ትርጉም፦ እኔን የበደለኝን ሰው ስም ከመጽሐፌ እሰርዛለሁ

• ከመጽሐፌ

ይህ መጽሐፍ ሙሴ የሚናገረው የእግዚአብሔር (ያህዌ) መጽሐፍ ነው። የመጽሐፉ ባለበት እግዚአብሔር (ያህዌ) ነው።

• ነገር ግን በምጐበኝበት ቀን ኃጢአታቸውን አመጣባቸዋለሁ አለው

ነገር ግን እኔ እነርሱን የምቀጣበት ጊዜ ሲደርስ ስለ ኀጢአታቸው የምቀጣው እኔ እግዚአብሔር ነኝ

• እግዚአብሔር ሕዝቡን ቀሠፈ

በምን ዓይነት ሁኔታ ህዝቡን እንደቀሰፈ አልተገለጸም ነገር ግን በበሽታ ሊሆን ይችላል። አማራጭ ትርጉም፦ እግዚአብሔር በሕዝቡ ላይ ከባድ በሽታ ላከ

• አሮን የሠራውን ጥጃ ስለ ሠሩ

የጥጃ ምስል ጣኦት የሰራው አሮን ቢሆንም ያንን የጥጃ ምስል ጣኦት አሮን እንዲሰራው ያስገደዱት ህዝቡ ነበሩ። አማራጭ ትርጉም፦ አሮን የጥጃ ምስል ጣኦት እንዲሰራ ህዝቡ በማስገደዳቸው