am_tn/exo/32/05.md

852 B

• አሮንም ባየው ጊዜ

ይህ ግልጽ ያልሆነ አባባል ነውና ግልጽ ማድረግ አስፈላጊ ነው። አሮን የእስራኤል ህዝብ ያደረገውን ባየ ጊዜ ወይም አሮን የሰራውን የወርቅ ጥጃ ባየ ጊዜ በሚል መተርጎም ይቻላል።

• ሊዘፍኑም ተነሡ

በአማርኛችን የዚህ ሀረግ ትርጉም በጣም ተደብቋል። “ሊዘፍኑም ተነሡ” የሚለው ተራ ዘፈን ሳይሆን ከሰው ባህርይ የወጣ ተግባር ሲፈጽሙ ነበር። ከበሉና ከጠጡ በኋላ ራሳቸውን መቆጣጠር አቅቷቸው በሜዳ ላይ ይሰስኑ፥ ይዳሩና ይዘሙቱ ነበር። የእንስሳነት ባህርይ ተላብሰው ልቅ ወሲብ ይፈጽሙ ነበር ማለት ነው።