am_tn/exo/31/12.md

1.8 KiB

• ሰንበቶቼን ፈጽሞ ጠብቁ

እግዚአብሔር በሙሴ በኩል ለእስራኤላውያን የሚነግራቸው የሰንበት ቀን በማክበር እርሱን እንድታዘዙ ነው።አማራጭ ትርጉም፦ “የሰንበት ቀን በማክበር እኔን መታዘዝ አለባችሁ”

• በእኔና በእናንተ ዘንድ ለልጅ ልጃችሁ ምልክት ነው

ከትውልድ እስከ ትውልድ ድረስ ወይም እስከ ልጅ ልጃችሁ ድረስ ምልክት ይሆናል

• እኔ የምቀድሳችሁ እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ታውቁ

እግዚአብሔር ለራሱ የለያችሁ ወይም የመረጣችሁ ሰዎች ናችሁ

• ለእናንተ ቅዱስ ነውና ሰንበትን ጠብቁ

የሰንበት ቀን ማክበር ቅዱስ ተግባር ስለሆነ ሰንበቴን አክብሩ

• የሚያረክሰውም ሰው

ሰንበትን ማክበር የማይፈልግ ወይም የሰንበት ቀን አክብሮት የሚሽር ሰው ወይም ትኩረት የማይሰጥና የሚንቅ ሰው

• ሁሉ ፈጽሞ ይገደል

በአድራጊ ግስ፦ ይህን ሰው ግደሉ ወይም ከመካከላችሁ አስወግዱ ወይም ይህ ሰው በሞት ይቀጣ

ከሕዝቡ መካከል ተለይቶ ይጥፋ

ይህ አባባል በተለያዩ መንገዶች ልተረጎም ይችላል

  1. እግዚአብሔር ይህን ሰው ከህዝቡ መካከል ይለየዋል ወይም እንደራሱ ህዝብ አይቆጥረውም
  2. እናንተ እስራኤላውያን ይህን ሰው ከመካከላችሁ ለዩ ወይም አስወግዱ
  3. እናንተ እስራኤላውያን ይህን ሰው ያለ ርህራሄ ግደሉት

• ሰባተኛው ቀን

ቀን 7 ወይም የሳምንቱ 7ኛ ቀን