am_tn/exo/29/03.md

1.0 KiB

አጠቃላይ ዕይታ፦

እግዚአብሔር (ያህዌ) ለሙሴ መናገሩን ይቀጥላል

• በአንድ ሌማትም ታደርጋቸዋለህ

“ሌማት” የተባለው የዳቦ/የቂጣ/የእንጀራ/ ወይም ሌላ ምግብ ማስቀመጫ የሚያመለክት ነው። አማራጭ ትርጉም፦ ሁሉንም በመሶብ ወይም በቅርጫት መሳይ ነገር ታስቀምጣቸዋለህ/ ታኖራቸዋለህ/

• ከወይፈኑና ከሁለቱ አውራ በጎች ጋር በሌማቱ ታቀርባቸዋለህ

በዚህ ክፍል “ታቀርባቸዋለህ” የሚለው መስዋዕት ማቅረብን የሚመለከት ነው። በሌላ አገላለጽ፦ አንድ ኰርማ/ወይፈን/ እና ሁለቱን አውራ በጎች በምትሠዋበት ጊዜ ለእኔ መባ/መስዋዕት/ አድርገህ አቅርብልኝ/ሰዋልኝ/

• መገናኛው ድንኳን

በሌላ ስሙ የማደሪያ ድንኳን ተብሎ ይታወቃል (ዘጸአት 27፡21 ተመልከት)