am_tn/exo/27/17.md

1.2 KiB

አጠቃላይ ምልከታ፦

እስራኤላውያን ምን ማድረግ እንዳለባቸው እግዚአብሔር በሙሴ በኩል መናገሩን ቀጥሏል።

• የአደባባዩ ርዝመት መቶ ክንድ ስፋቱም አምሳ ክንድ ይሁን

የድንኳኑ አደባባይ ርዝመቱ አርባ ስድስት ሜትር የጐኑ ስፋት ሃያ ሶስት ሜትር ሆኖ ይሰራ

• መጋረጃውም ከጥሩ በፍታ

መጋረጃው ከጥሩ /ከቀጭን/ የሐር ጨርቅ/ክር/ የተሰራ ይሁን ወይም መጋረጃውን ከጥሩ/ከቀጭን/ የሐር ጨርቅ/ክር/ ሥራ

• ለማገልገል ሁሉ የማደሪያው ዕቃ ሁሉ፥ ካስማዎቹም ሁሉ የአደባባዩም ካስማዎች ሁሉ፥ የናስ ይሁኑ

በድንኳኑ ውስጥ የሚገኙት ለማናቸውም አገልግሎት የሚውሉ የመገልገያ ዕቃዎችን ሁሉ፥ የድንኳኑንና የአደባባዩ ካስማዎችን ሁሉ ከነሐስ ብረት ሥራቸው።

• ካስማዎች

ከብረት ወይም ከእንጨት የተሰሩ በአንድ በኩል ሹል የሆኑ ድንኳን ለመወጠር የሚያገለግሉ ናቸው