1.2 KiB
1.2 KiB
• አደራ ቢያኖር
እንዳይጠፋበት ወይም እንዳይሰረቅበት በአደራ ቢያስቀምጥ
• ከቤቱም ቢሰረቅ
በሌላ አገላለጽ፦ አንድ ሰው ወይም ሌባ ቢሰርቀው
• ሌባው ቢገኝ
በሌላ አገላለጽ፦ የሰረቀውን ሰው ብታገኘው ወይም ብታገኘው
• ሌባውም ባይገኝ ባለቤቱ ወደ ፈራጆች ይቅረብ
ሌባው ካልተገኘ ግን ዕቃውን በዐደራ የተቀበለው ሰው ዳኞች ፊት ይቅረብ /ይምጣ/
• እጁንም በባልንጀራው ከብት ላይ እንዳልዘረጋ ይማል
“እጁን . . . እንዳልዘረጋ” የሚለው ዘይቤያዊ አነጋገር ነው። ይህን ዘይቤያዊ እነጋገር በተመሳሳይ ዘይቤያዊ ንግግር መትርጎም የሚቻል ከሆነ መተረጎም ጥሩ ነው። አማራጭ ትርጉም፦ የዚያን ሰው ንብረት ራሱ አለመስረቁን በመሐላ ያረጋግጥ
• ክርክራቸው ወደ ፈራጆች ይድረስ
በሁለቱ መካከል ክርክር ቢነሣ ባለ ጉዳዮቹ ነገሩን ለዳኞች ያቅርቡት