1.7 KiB
1.7 KiB
አጠቃላይ ዕይታ፦
እግዚአብሔር (ያህዌ) ህጉን በሙሴ በኩል ለእስራኤላውያን መናገሩን ሲቀጥል እናያለን
• ቢሰርቅ
በሌላ አገላለጽ፦ አንድ ሰው ሌባ ሆኖ ቢገኝ ወይም አንድ ሰው ሰርቆ ቢገኝ
• ሌባው ቤት ሲምስ ቢገኝ
በሌላ አገላለጽ፦ አንድ ሌባ የአንድ ሰው ቤት ሰብሮ ቢገባ
• እርሱም እስኪሞት ቢመታ
በሌላ አገላለጽ፦ አንድ ሰው ቢመታውና ሌባው ቢሞት
• በመታው ሰው ላይ የደም ዕዳ አይሆንበትም
በሌላ አገላለጽ፦ ተከላካዩ ወይም ሌባውን መቶ የገደለው ሰው ለፈሰሰው ደም ወይም በመግደሉ ተጠያቂ አይሆንም
• ፀሐይ ግን ከወጣችበት የደም ዕዳ አለበት
በሌላ አባባል፦ ፀሐይ ከወጣ በኋላ ወይም ብርሃን እያለ ሌባው ተመትቶ ቢገደል ግን ተከላካዩ በግድያው ተጠያቂ ይሆናል
• ሌባው የሰረቀውን ይመልስ
ሌባው የሰረቀውን መክፈል አለበት ወይም ሌባው በሰረቀው ንብረት ምትክ ክፊያ መስጠት አለበት
• የሚከፍለውም ቢያጣ ስለ ሰረቀው ይሸጥ
ምንም ከሌለው ግን የሰረቀውን ይከፍል ዘንድ ራሱ በባርነት ይሸጥ
• የሰረቀው ደኅና ሆኖ በእጁ ቢገኝ
ሌባው የሰረቀው እንስሳ ሕያው ሆኖ ቢገኝ ወይም በሕይወት ቢገኝ
• የሰረቀውን ያህል ሁለት እጥፍ ይክፈል
ለያንዳንዱ እንስሳ ዕጥፍ ዋጋ ወይም ሁለት እንስሳ ይክፈል