am_tn/exo/19/03.md

1.8 KiB

• የያቆብ ቤት

“የያዕቆብ ቤት” የሚለው የያዕቆብን ቤተሰብ እና ትውልዱን የሚመለከት ነው። አማራጭ ትርጉም፦ የያዕቆብ ተወላጆች ለሆኑት

• ለያቆብ ቤት . . . ለእስራኤልም ልጆች

“የእስራኤል ልጆች” የሚለው ሀረግ የሚገልጸው “የያዕቆብ ቤት” የሚለውን የሚያብራራ ነው።

• በንስርም ክንፍ እንደ ተሸከምኋችሁ

እግዚአብሔር ለእስራኤላውያን ያደረገውን ጥበቃና ጥንቃቄ ሲገልጽ እርሱ ንስር እንደ ሆነና እነርሱን በክንፉ እንደ ተሸከማቸው አድርጎ ይገልጻል። አማራጭ ትርጉም፦ ንስር ጫጩቶችዋን በክንፎችዋ እንደምትሸከም እኔም እናንተን እንዴት እንደተሸከምኳችሁ

• ቃሌን በእውነት ብትሰሙ

“ቃሌን ብትሰሙ” የሚለው እንዲሁ መስማት ብቻ ሳይሆን መታዘዝንም ይጨምራል። በሌላ አገላለጽ፦ ቃሌን ብትሰሙና ለእኔም ብትታዘዙ

• ኪዳኔንም ብትጠብቁ

ቃል ኪዳኔ የምጠይቃችሁን ነገር ብትፈጽሙ

• ርስት ትሆኑልኛላችሁ

የእኔ ርስት ወይም ሀብት ትሆናላችሁ

• የካህናት መንግስት . . . ትሆኑልኛላችሁ (ተለዋጭ ዘይቤ)

እግዚአብሔር ህዝቡ ካህናት እንደሆኑ ይናገራል። አማራጭ ትርጉም፦ የመንግስት ህዝብ የሆናችሁ ለእኔ እንደ ካህናት ናችሁ ወይም የመንግስት ህዝብ የሆናችሁ እናንተ ለእኔ ካህናት የሚሰሩትን የምትሰሩ ናችሁ