am_tn/exo/13/14.md

1.1 KiB

• በሚመጣው ጊዜ ልጅህ፦ ይህ ምንድር ነው? ብሎ በጠየቀህ ጊዜ እንዲህ ትለዋለህ

በሌላ አገላለጽ፦ “በሚመጡት ዘመናት ልጆችህ የዚህ ሥርዓት ትርጉም ምንድን ነው” ብለው ቢጠይቁህ፥ እንዲህ ብለህ ታስረዳቸዋለህ

• እግዚአብሔር በብርቱ እጅ

ምክንያቱም እግዚአብሔር በታላቅ ኀይሉ

• የባርነት ቤት

ህዝቡ በአንድ ቤት ታጉሮ እንደነበር ዓይነት አነጋገር የያዘ ዘይቤ ነው። አማራጭ ትርጉም፦ “በባርነት የነበራችሁበትን ሁኔታ ወይም ሕይወት”

• በእጅህ እንደ ምልክት፥ በዓይኖችህም መካከል እንደ ተንጠለጠለ ነገር ይሁንልህ

እስራኤላውያን በዓሉን ወይም የፋሲካ በዓል ሲያከብሩ እነዚህን ሁለት የሚታዩ ምልክቶችን እንድያደርጉ ሙሴ ያሳስባቸዋል (ተነጻጻሪ ዘይቤ፤ ለተመሳሳይ አገላለጽ 13፡8-10 ተመልከት)