am_tn/exo/02/23.md

879 B

• አለቀሱ

ከመከራቸውና ከጭንቃቸው የተነሳ ማልቀሳቸውን የሚያሳይ ነው

• ጩኸታቸው ወደ እግዚአብሔር ወጣ

የእስራኤላውያን ጩኸት እግር እንዳለው ሰው ወደ እግዚአብሔር እንደተጓዘ ወይም እንደሄደ በሰውኛ ዘይቤ የተነገረ ነው። በቀጥተኛ ዐረፍተ ነገር ሲነገር “እግዚአብሔር ጩኸታቸውን ሰማ” የሚል ነው።

• እግዚአብሔር . . . ቃል ኪዳኑን አሰበ

ይህ አባባል በዕብራውያን ዘንድ የተለመደ ነው። ሰው አንድን ነገር ረስቶ እንደገና እንደሚያስብ የተነገረ ዘይቤያዊ ንግግር ነው። በሌላ አገላለጽ፦ “እግዚአብሔር የገባውን ቃል ኪዳን አሰበ”።