am_tn/exo/02/01.md

776 B

• በዚያን ጊዜ

በዕብራይስጡና በቀድሞ አማርኛ ትርጉም (በ1954 ትርጉም) ይህ አገናኝ ሀረግ የለም። ነገር ግን በአንዳንድ እንግሊዘኛና በሌሎች አማርኛ ትርጉሞች እንደ አገናኝ ሀረግ የገባ ነው። ይህ አገናኝ ሀረግ አዲስ ሀሳብ ሲጀመር ወይም አንድ ታሪክ አልቆ ሌላ ታሪክ ሲጀመር የሚያሳይ ነው። ንጉሱ የዕብራውያን ወንድ ልጆች እንዲገደሉ ባዘዘበት ጊዜ ሌላ ታሪክ ሲከሰት ያሳየናል። ተርጓሚዎች በቋንቋቸው እንደዚህ ያሉ እገናኝ ሀረጎች ወይም ቃላት መኖሩን ማረጋገጥ ይጠበቅባቸዋል።