am_tn/deu/32/46.md

1.9 KiB

ተናገራቸው

“ሙሴ ለእስራኤል ሕዝብ ተናገራቸው”

በልባችሁ አኑሩት

ይህ የአነጋገር ዘይቤ ነው። አ.ት፡ “ለ -- ትኩረት ስጡ” ወይም “ስለ -- አስቡ” (የአነጋገር ዘይቤ የሚለውን ተመልከት)

መስክሬላችኋለሁ

ሊሆኑ የሚችሉ ትርጉሞች 1) ባይታዘዙ እግዚአብሔር በእስራኤላውያን ላይ ምን እንደሚያደርግባቸው የተናገረውን ለማመልከት “መስክሬላችኋለሁ” ማለቱን ያመለክታል ወይም 2) እንዲያደርጉት እግዚአብሔር ያዘዛቸውን ለማመልከት “አዝዥችኋለሁ” የሚሉት ናቸው

ልጆቻችሁ

“ልጆቻችሁና ተወላጆቻችሁ”

ይህ ነው

“ይህ ሕግ ነው”

አላስፈላጊ ነገር አይደለም

ይህ ምጸት በአዎንታዊነት ሊነገር ይችላል። አ.ት፡ “በጣም ጠቃሚ የሆነ ነገር” (ምጸት የሚለውን ተመልከት)

እርሱ ሕይወትህ ስለሆነ

የነገር ስም የሆነው “ሕይወት” “መኖር” ወደሚል ግሥ ሊተረጎም ይችላል። ሕግን ራሱን የሚወክለውን የመታዘዝን ፈሊጣዊ አነጋገር ግልጽ ማድረግ ይኖርብህ ይሆናል። አ.ት፡ “ብትታዘዝው በሕይወት ትኖራለህና” (ፈሊጣዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)

ቀኖችህ እንዲረዝሙ

ረጅም ቀናት የረጅም ሕይወት ዘይቤአዊ አነጋገር ነው። እነዚህን ቃላት በዘዳግም 4፡26 ላይ እንዴት እንደተረጎምካቸው ተመልከት። አ.ት፡ “ረጅም ጊዜ መኖር እንድትችል” (ዘይቤአዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)