am_tn/deu/30/06.md

1.6 KiB

ልብህን ይገርዛል

ይህ በቀጥታ ሥጋን ማስወገድ አይደለም። ይህ ማለት እግዚአብሔር ኃጢአታቸውን ያስወግዳል፣ እርሱን እንዲወዱትና እንዲታዘዙትም ያስችላቸዋል ማለት ነው። (ዘይቤአዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)

በሙሉ ልብህና በሙሉ ነፍስህ

እዚህ ጋ “ልብ” እና “ነፍስ” የአንድን ሰው ውስጣዊ ማንነት የሚያመለክቱ ፈሊጣዊ አነጋገሮች ናቸው። እነዚህ ሁለቱ ሐረጎች በአንድ ላይ “ፍጹም” ወይም “በቅንነት” ለማለት ጥቅም ላይ ውለዋል። እነዚህን ቃላት በዘዳግም 4፡29 ላይ እንዴት እንደተረጎምካቸው ተመልከት። (ፈሊጣዊ አነጋገር እና Doublet የሚለውን ተመልከት)

የእግዚአብሔርን ድምፅ ታዘዝ

እዚህ ጋ “ድምፅ” ማለት እግዚአብሔር የሚናገረውን ማለት ነው። አ.ት፡ “እግዚአብሔር የሚናገረውን ታዘዝ” (ፈሊጣዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)

እነዚህን እርግማኖች ሁሉ በጠላቶችህ ላይ ያደርጋል

ሙሴ እርግማኖቹን አንድ ሰው በሌላው አናት ላይ ሊያደርግ እንደሚችለው ሸክም ወይም መሸፈኛ አድርጎ ይናገራል። አ.ት፡ “ጠላቶችህ በእነዚህ እርግማኖች ምክንያት እንዲሰቃዩ ያደርጋል” (ዘይቤአዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)