am_tn/deu/27/01.md

1.4 KiB

ዛሬ የማዛችሁን -- ትሻገራላችሁ

ሙሴ እንደ አንድ ቡድን አድርጎ የሚናገረው ለእስራኤላውያን ነው፣ ስለዚህ በሁለቱም አገባብ “አንተ” የሚለው ቃል ብዙ ቁጥር ነው። (See: Forms of You)

የማዛችሁን

እዚህ ጋ “እኔ” የሚያመለክተው ሙሴን ነው። ሽማግሌዎቹ ከሙሴ ጋር ተስማምተው በዚያ አሉ፣ ሆኖም ብቸኛው ተናጋሪ እርሱ ነው።

በኖራ ቅባው

ይህ ዓይነቱ በአብዛኛው የኖራ፣ አሸዋና ውሃ ድብልቅ ሲሆን በአንድ ነገር ላይ የሚቀባ ነው። ሲደርቅ አንድ ሰው በላዩ ላይ መጻፍ እንዲችል ጠንካራና ለስላሳ ገጽታ ይኖረዋል። አ.ት፡ “ቅባቸው” ወይም “ልትጽፍባቸው እንዲያስችሉህ አድርግ” (See: Assumed Knowledge and Implicit Information)

ወተትና ማር የምታፈስ ምድር

ይህ የአነጋገር ዘይቤ ነው። ይህንን በዘዳግም 6፡3 ላይ እንዴት እንደተረጎምከው ተመልከት። አ.ት፡ “ብዙ ወተትና ማር የሚፈስባት ምድር” ወይም “ለከብት እርባታና ለእርሻ ምርጥ የሆነች ምድር” (የአነጋገር ዘይቤ የሚለውን ተመልከት)