am_tn/deu/19/04.md

2.2 KiB

ሕጉ ይህ ነው

“መመሪያዎቹ እነዚህ ናቸው” ወይም “አቅጣጫዎቹ እነዚህ ናቸው”

ሌላውን የገደለ

“ሰው” የሚለው ቃል እንዳለበት ይታወቃል። አ.ት፡ “ሌላውን ሰው የገደለ ሰው” (See: Ellipsis)

ወደዚያ የሚሸሽ

“ከእነዚህ ከተሞች ወደ አንዱ የሚያመልጥ” ወይም “ከእነዚህ ከተሞች ወደ አንዱ የሚሮጥ”

ለመኖር

“ሕይወቱን ለማዳን”። የዚህ መግለጫ ሙሉ ትርጉም ግልጽ መደረግ ይችላል። አ.ት፡ “የሟች ቤተሰብ ተበቅለው እንዳይገድሉት” (See: Assumed Knowledge and Implicit Information)

ማንም ሳያውቅ ባልንጀራውን የሚገድል

እዚህ ጋ “ባልንጀራ” ማለት በአጠቃላይ የትኛውም ሰው ማለት ነው። አ.ት፡ “በድንገት ሌላውን ሰው የሚገድል የትኛውም ሰው”

አስቀድሞ ጥላቻ ሳይኖረው

“ነገር ግን ባልንጀራውን ከመግደሉ በፊት አልጠላው እንደሆነ”። ባልንጀራውን አስቦበት የሚገድልበት ምክንያት እንዳልነበረው ያመለክታል። (See: Assumed Knowledge and Implicit Information)

ለምሳሌ፣ አንድ ሰው እንጨት ለመቁረጥ ወደ ጫካ ቢሄድ

ደራሲው አንድ ሰው ሌላውን በድንገት የሚገድልበትን መላ ምታዊ ሁኔታ ይሰጣል። (See: Hypothetical Situations)

ብረቱ ከእጀታው ወልቆ

የመጥረቢያው የብረት ክፍል ከእንጨቱ እጀታ ወልቆ

ባልንጀራውን መትቶ ቢገድለው

ይህ ማለት የመጥረቢያው ራስ ባልንጀራውን መትቶ ገድሎታል ማለት ነው።

ከእነዚህ ከተሞች ወደ አንዲቱ -- ሕይወቱን ያድን

የሟቹ ሰው ቤተሰብ ምናልባት ሊበቀሉት እንደሚሞክሩ ያመለክታል። በዚያ ያሉት ሰዎች ጥበቃ እንዲያደርጉለት እርሱን የገደለው ሰው ከእነዚህ ከተሞች ወደ አንዲቱ መሸሽ ይችላል (See: Assumed Knowledge and Implicit Information)