am_tn/deu/18/20.md

1.4 KiB

በትዕቢት ቃልን የሚናገር

“መልዕክት ለመናገር የሚደፍር” ወይም “በዕብሪተኝነት መልዕክት የሚናገር”

በስሜ

እዚህ ጋ “ስሜ” የሚያመለክተው ራሱን እግዚአብሔርንና ሥልጣኑን ነው። አ.ት፡ “ለእኔ” ወይም “በእኔ ሥልጣን” (ፈሊጣዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)

ቃልን

“መልዕክትን”

በሌሎች አማልክት ስም የሚናገር

እዚህ ጋ “ስም” የሚወክለው አማልክቱን ራሳቸውን ወይም ሥልጣናቸውን ነው። ይህ ማለት ሐሰተኞቹ አማልክት አንድን መልዕክት እንዲናገር እንደ ነገሩት ነቢዩ ያስታውቃል ማለት ነው። (ፈሊጣዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)

በልብህ እንዲህ ትላለህ

እዚህ ጋ “ልብ” የሚወክለው የሰውን አሳብ ነው። አ.ት፡ “ራስህን ትጠይቃለህ” ወይም “ለራስህ ትናገራለህ” (ፈሊጣዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)

መልዕክቱን እግዚአብሔር እንዳልተናገረ እንዴት እንለያለን?

“ነቢዩ የሚናገረው መልዕክት ከእግዚአብሔር መሆኑን እንዴት እናውቃለን? እዚህ ጋ “እኛ” የሚያመለክተው የእስራኤልን ሕዝብ ነው።