am_tn/deu/16/01.md

1.1 KiB

የአቢብ ወር

ይህ በዕብራውያን የቀን አቆጣጠር የመጀመሪያው ወር ነው። እርሱ እግዚአብሔር የእስራኤልን ሕዝብ ከግብፅ አውጥቶ ያመጣበትን ጊዜ ያስታውሳል። በምዕራባውያኑ አቆጣጠር በመጋቢት መጨረሻና በሚያዝያ መጀመሪያ አካባቢ ነው። (የዕብራውያን ወራት እና ስሞች እንዴት እንደሚተረጎሙ የሚለውን ተመልከት)

ፋሲካን ጠብቀው

“ፋሲካን ጠብቀው” በዓሉን ማክበርና የፋሲካን ምግብ መብላት እንዳለባቸው ያመለክታል። አ.ት፡ “የፋሲካን ምግብ አክብር” ወይም “የፋሲካን ምግብ ብላ” (See: Assumed Knowledge and Implicit Infor- mation)

ፋሲካን ትሠዋለህ

እዚህ ጋ “ፋሲካ” የሚወክለው ለፋሲካ በዓል የሚሠዋውን እንስሳ ነው። አ.ት፡ “ለፋሲካ መሥዋዕት ታቀርባለህ” (ፈሊጣዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)