am_tn/deu/15/12.md

1.5 KiB

ወንድምህ

እዚህ ጋ “ወንድም” ማለት ወንድ ይሁን ሴት በአጠቃላይ እስራኤላዊ የሆነ ማለት ነው። አ.ት፡ “አንድ እስራኤላዊ ጓደኛህ” ወይም “አንድ ዕብራዊ ጓደኛህ” (ተባዕታዊ ቃል ሴቶችን ሲጨምር የሚለውን ቃል ተመልከት)

ለአንተ የተሸጠ

አንድ ሰው ዕዳውን መክፈል ባይችል አንዳንድ ጊዜ የተበደረውን ለመክፈል ራሱን ለባርነት ይሸጥ ነበር። ይህ በአድራጊ ድምፅ ሊነገር ይችላል። አ.ት፡ “ራሳቸውን ለአንተ የሸጡ” (አድራጊ ወይም ተደራጊ ድምፅ የሚለውን ተመልከት)

ስድስት ዓመት

“6 ዓመት” (ቁጥሮች የሚለውን ተመልከት)

ሰባተኛ ቁጥር

“7 ዓመት”። ይህ “ሰባተኛ” የሰባት ደረጃን አመልካች ቁጥር ነው። (ደረጃን አመልካች ቁጥር የሚለውን ተመልከት)

ባዶ እጁን እንዲሄድ አታድርግ

ለራሱ ወይም ለቤተሰቡ የሚያቀርበው አስፈላጊ ነገር የሌለው ሰው እጆቹ ባዶ እንደሆኑ ተደርጎ ተነግሯል። አ.ት፡ “ለእርሱና ለቤተሰቡ የሚያቀርበው እንዲኖረው ሳትሰጠው እንዲሄድ አታድርገው” (ዘይቤአዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)

በልግስና ስጠው

“በደግነት ስጠው”