am_tn/deu/11/18.md

3.2 KiB

እነዚህን ቃሎቼን በልባችሁና በነፍሳችሁ ውስጥ አኑሩ

ሙሴ የሚያዝዘውን ዘወትር የሚያስብና የሚያመዛዝን ሰው ልቡና ነፍሱ መያዣ ዕቃ እንደሆኑና የሙሴ ቃላት መያዣውን እንደሚሞላ አንዳች ይዘት ተደርጎ ተነግሯል። አ.ት፡ አ.ት፡ “የምነግራችሁን እነዚህን ቃላት ለማስታወስ በጣም ተጠንቀቁ” (ዘይቤአዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)

እነዚህን ቃሎቼን

“የሰጠኋችሁን እነዚህን ትዕዛዛት”

ልባችሁንና ነፍሳችሁን

እዚህ ጋ “ልብ” እና “ነፍስ” የሚወክሉት የአንድን ሰው አዕምሮ ወይም አሳብ ነው። (ፈሊጣዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)

እሰሯቸው

“እነዚህን ቃላት እሰሯቸው”። ይህ ፈሊጣዊ አነጋገር በብራና ላይ የሚጽፍን፣ ብራናውን በትንሽ ኪስ መሰል ማስቀመጫ የሚከተውንና የሚያስረውን ሰው ይወክላል። ይህ ፈሊጣዊ አነጋገር በሌላ መልኩ ሕዝቡ የሙሴን ትዕዛዛት ለመታዘዝ መጠንቀቅ አለበት የሚል ትርጉም ያለው ዘይቤአዊ አነጋገር ሊሆን ይችላል። ተመሳሳዮቹን ሐረጎች በዘዳግም 6፡8 ላይ እንዴት እንደተረጎምካቸው ተመልከት። (ፈሊጣዊ አነጋገር እና ዘይቤአዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)

በእጅህ ላይ እንደ ምልክት

“ሕጌን እንድታስታውስ እንደሚያደርግህ አንዳች ነገር”

በዐይኖችህ መካከል እንደ ክታብ ይሁኑልህ

“ቃሎቼ በዐይኖችህ መካከል እንደ ክታብ ይሆኑልህ”። ይህ የሙሴን ቃላት በብራና ላይ የሚጽፍ፣ ብራናውን በትንሽ ኪስ መሰል ማስቀመጫ የሚከትና በዐይኖቹ መካከል የሚያስርን ሰው የሚወክል ፈሊጣዊ አነጋገር ነው። ይህ ፈሊጣዊ አነጋገር በሌላ መልኩ ያ ሰው ሙሴ የሚያዘውን ትዕዛዝ ሁሉ ለመታዘዝ መጠንቀቅ አለበት የሚል ትርጉም ያለው ዘይቤአዊ አነጋገር ሊሆን ይችላል። በዘዳግም 6፡8 ላይ ተመሳሳዮቹን ሐረጎች እንዴት እንደተረጎምካቸው ተመልከት። (ፈሊጣዊ አነጋገር እና ዘይቤአዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)

ክታቦች

አንድ ሰው በግምባሩ ላይ የሚያስራቸው ጌጣ ጌጦች

በቤትህ ስትቀመጥ፣ በመንገድ ስትሄድ፣ ስትተኛና ስትነሣ

“በቤትህ” እና “በመንገድ” የሚሉትን የተለያዩ ቦታዎች መጠቀምና ተቃራኒዎቹ “ስትተኛ” እና “ስትነሣ” ሁልጊዜ በሁሉ ቦታ ማለትን ይወክላሉ። የእስራኤል ሕዝቦች በየትኛውም ጊዜና በየትኛውም ቦታ የእግዚአብሔርን ትዕዛዛት ማጥናትና ለልጆቻቸው ማስተማር ነበረባቸው። (See: Merism)