am_tn/deu/11/13.md

1.6 KiB

ብታደርጉ ይሆናል

ይህ ማለት እስራኤላውያን እግዚአብሔር ያዘዛቸውን ከታዘዙ እርሱ የሰጣቸውን ተስፋ ይፈጽምላቸዋል።

እኔ የማዝህን

እዚህ ጋ “እኔ” የሚያመለክተው ሙሴን ነው።

በሙሉ ልብህና በሙሉ ነፍስህ

“በሙሉ ልብህ” የሚለው የአነጋገር ዘይቤ “በፍጹም” ማለት ሲሆን “በ . . . ነፍስህ” ማለት “በሁለንተናህ” ማለት ነው። እነዚህ ሁለት ሐረጎች ተመሳሳይ ትርጉም አላቸው። ይህንን በዘዳግም 4፡29 ላይ እንዴት እንደተረጎምካቸው ተመልከት። አ.ት፡ “በሁለንተናህ” ወይም “በሙሉ ኃይልህ” (የአነጋገር ዘይቤ እና Doublet የሚለውን ተመልከት)

ለምድርህ ዝናብን በወቅቱ እሰጣለሁ

“በተገቢው ወቅት በምድርህ ላይ ዝናብ እንዲዘንብ አደርጋለሁ”

እሰጣለሁ

እዚህ ጋ “እኔ” የሚያመለክተው እግዚአብሔርን ነው። ይህ በሦስተኛ መደብ ሊነገር ይችላል። አ.ት፡ “እግዚአብሔር ይሰጣችኋል” ወይም “እርሱ ይሰጣችኋል”

የመጀመሪያውንና የኋለኛውን ዝናብ

ይህ የሚያመለክተው በመጀመሪያ በዘር ወቅት የሚዘንበውን ዝናብና ሰብሉን ለምርትነት የሚያበቃውን ዝናብ ነው። አ.ት፡ “የመከርንና የፀደይን ዝናብ” ወይም “ዝናብን በወቅቱ”