am_tn/deu/10/20.md

1.6 KiB

እርሱን አምልከው

“ልታመልከው የሚገባህ እርሱን ነው”

ከእርሱ ጋር ተጣበቅ

ከእግዚአብሔር ጋር መልካም ግንኙነት መኖርና በእርሱ ላይ ሙሉ በሙሉ መታመን ከእግዚአብሔር ጋር መጣበቅ በሚል መልኩ ተነግሯል። አ.ት፡ “በእርሱ ላይ መታመን አለብህ” ወይም “ልትታመንበት የሚገባህ በእርሱ ላይ ነው” (ዘይቤአዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)

በስሙም ማል

በእግዚአብሔር ስም መማል ማለት እግዚአብሔርን የተደረገው መሐላ መሠረት ወይም ኃይል ማድረግ ማለት ነው። እዚህ ጋ፣ “ስም” የሚወክለው እግዚአብሔርን ራሱን ነው። በዘዳግም 6፡13 ላይ ተመሳሳዩን ሐረግ እንዴት እንደተረጎምከው ተመልከት። አ.ት፡ “ትምላለህ፣ እግዚአብሔር እንዲያጸናውም ትጠይቀዋለህ” ወይም “በምትምልበት ጊዜ ስሙን ትጠራለህ” (ፈሊጣዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)

ዐይኖችህ ያዩትን

እዚህ ጋ፣ “ዐይኖች” የሚያመለክተው የሰውን ሁለንተና ነው። አ.ት፡ “አንተ ራስህ ያየኸውን” (See: Synecdoche)

እርሱ ምስጋናህ ነው

ሊሆኑ የሚችሉት ትርጉሞች 1) “ልታመሰግን የሚገባህ እርሱን ነው” ወይም 2) “አንተ ስለምታመሰግነው ሌሎች ሕዝቦች ያመሰግኑሃል”