am_tn/deu/09/01.md

1.7 KiB

እስራኤል ሆይ፣ ስማ

“እስራኤል” የሚለው ቃል የእስራኤልን ሕዝብ የሚመለከት ፈሊጣዊ አነጋገር ነው። አ.ት፡ “የእስራኤል ሕዝብ ሆይ፣ ስማ” (ፈሊጣዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)

ለመውረስ

“መሬታቸውን ለመውሰድ”

እስከ ሰማይ ድረስ የተመሸጉትን

ይህ ከተሞቹ በጣም ሰፊና ጠንካራ በመሆናቸው ምክንያት ሕዝቡ መፍራታቸውን አጽንዖት ለመስጠት የተደረገ ግነት ነው። በዘዳግም 1፡28 ላይ ተመሳሳዩን ቃላት እንዴት እንደተረጎምካቸው ተመልከት። አ.ት፡ “ሰማይ የሚደርሱ የሚመስሉ ግንቦች ነበሯቸው” (ግነት እና ጥቅል አስተያየት የሚለውን ተመልከት)

የዔናቅ ልጆች

በጣም ረጃጅምና ኃያላን የነበሩ የዔናቅ ሕዝብ ተወላጆች ናቸው። ተመሳሳዮቹን ቃላት በዘዳግም 1፡28 ላይ እንዴት እንደተረጎምካቸው ተመልከት።(See: Assumed Knowledge and Implicit Information እና ስሞች እንዴት እንደሚተረጎሙ የሚለውን ተመልከት)

በዔናቅ ልጆች ፊት ማን መቆም ይችላል?

ይህ ማለት የዔናቅ ልጆች ኃያላን በመሆናቸው ሰዎች ይፈሯቸው ነበር። ይህ ምላሽ የማይፈልግ ጥያቄ እንደ መግለጫ ሊተረጎም ይችላል። አ.ት፡ “በዔናቅ ልጆች ፊት ራሱን መከላከል የሚችል አልነበረም” (ምላሽ የማይፈልግ ጥያቄ የሚለውን ተመልከት)