am_tn/deu/08/13.md

1.5 KiB

መንጋዎችህ

“የከብትህ፣ የበግና የፍየል መንጋህ”

መብዛት

በቁጥር እጅግ መጨመር

ያለህ ሁሉ ሲበዛልህ

ይህ በአድራጊ ድምፅ ሊነገር ይችላል። አ.ት፡ “በጣም ብዙ ነገሮች አሉህ” ወይም “በጣም ብዙ ንብረት አለህ” (አድራጊ ወይም ተደራጊ ድምፅ የሚለውን ተመልከት)

ልብህ ይነሣሣል

እዚህ ጋ “ልብ” የሚወክለው ውስጠኛውን ሰው ነው። መታበይና ከእንግዲህ እግዚአብሔርን ያለመታዘዝ እንደ ሰው ልብ መነሣሣት ሆኖ ተነግሯል። በዘዳግም 8፡12 ላይ ተመሳሳዩን ሐረግ እንዴት እንደተረጎምከው ተመልከት። አ.ት፡ “ትታበያለህ፣ ከእንግዲህም እግዚአብሔርን አትታዘዝም” (ፈሊጣዊ አነጋገር እና ዘይቤአዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)

ያወጣህን

ሙሴ ለእስራኤላውያን ስለ እግዚአብሔር የሚያውቁትን ማስታወስ ጀምሯል (ለይቶ ማሳወቅ ማሳወቅን ወይም ማስታወስን ሲቃረን የሚለውን ተመልከት)

ከባርነት ቤት ያወጣህ

ይህ በግብፅ በባርነት የነበሩበትን ጊዜ የሚያመለክት ዘይቤአዊ አነጋገር ነው። አ.ት፡ “ባሪያዎች ከነበራችሁበት ስፍራ” (ዘይቤአዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)