am_tn/deu/06/20.md

1.7 KiB

ያዘዛችሁ የቃል ኪዳኑ ድንጋጌዎች ምንድናቸው

በዚህ ጥያቄ “የቃል ኪዳን ድንጋጌዎች” ትርጉማቸውንና ዓላማቸውን ይወክላሉ። አ.ት፡ “የታዘዙት የቃል ኪዳን ድንጋጌዎች ለአንተ ምን ትርጉም አላቸው” ወይም “የታዘዝከውን የቃል ኪዳን ድንጋጌዎች መታዘዝ የሚኖርብህ ለምንድነው”(ፈሊጣዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)

ልጅህ

ይህ የሚያመለክተው ሙሴ የእግዚአብሔርን ቃል የሚነግራቸው የትልልቆቹ እስራኤላውያንን ልጆች ነው።

በጽኑ እጅ

እዚህ ጋ “ጽኑ እጅ” የሚያመለክተው የእግዚአብሔርን ኃይል ነው። ይህንን በዘዳግም 4፡34 ላይ እንዴት እንደተረጎምከው ተመልከት፡ አ.ት፡ “በጽኑ ኃይሉ” (ዘይቤአዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)

በቤቱ ሁሉ

እዚህ ጋ “ቤቱ” የሚለው ፈሊጣቂ አነጋገር የሚያመለክተው የእግዚአብሔርን ሕዝብ ነው። አ.ት፡ “በሕዝቡ ሁሉ ላይ” (ፈሊጣዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)

በዐይኖቻችን ፊት

እዚህ ጋ “ዐይኖቻችን” የሚለው ቃል የሚያመለክተው የሰውን ሁለንተናውን ነው። አ.ት፡ “ልናያቸው በምንችልበት” (See: Synecdoche)

ሊያስገባን

የዚህ መግለጫ ሙሉ ትርጉም መብራራት ይችላል። አ.ት፡ “ወደ ከነዓን ሊያስገባን” (See: Assumed Knowledge and Implicit Information)