am_tn/deu/03/19.md

1.5 KiB

እግዚአብሔር ለወንድሞቻችሁ እረፍትን እስኪሰጥ

ጸሐፊው የማረፍን ችሎታ በስጦታ እንደሚሰጥ ቁሳዊ አካል አድርጎ ይናገራል። በተጨማሪም፣ “ማረፍ” የሚለው ቃል ጦርነት የሌለበትን ሰላማዊ ኑሮ የሚያመለክት ዘይቤአዊ አነጋገር ነው። አ.ት፡ “ወድሞቻችሁ እንዲያርፉ እግዚአብሔር ይፈቅዳል” ወይም “በጦርነት መዋጋትን አቁመው በሰላም እንዲኖሩ እግዚአብሔር ለወንድሞቻችሁ ይፈቅዳል” (ዘይቤአዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)

ከዮርዳኖስ ማዶ

ይህ ከእስራኤል በስተምስራቅ ከዮርዳኖስ ወንዝ ባሻገር ያለውን ምድር ያመለክታል። ሙሴ ይህንን በሚናገርበት ጊዜ ከዮርዳኖስ በስተምስራቅ ነበር። በዘዳግም 1፡1 ላይ እነዚህን ቃላት እንዴት እንደተረጎምካቸው ተመልከት። አ.ት፡ “ከዮርዳኖስ ወንዝ በስተምስራቅ”

ከዚያም ትመለሳላችሁ

እግዚአብሔር ለእነዚህ ሦስት ነገዶች ምድራቸውን እንዲወርሱ ከመፍቀዱ በፊት ሌሎቹ ነገዶች መሬታቸውን መውረስ እንዳለባቸው ሙሴ አጽንዖት ይሰጣል። “የምትመለሱት ከዚያ በኋላ ብቻ ነው”።