am_tn/deu/02/36.md

1.4 KiB

አሮዔር

ይህ በአርኖን ወንዝ ሰሜናዊ ዳርቻ የሚገኝ ከተማ ስም ነው። (ስሞች እንዴት እንደሚተረጎሙ የሚለውን ተመልከት)

የአርኖን ሸለቆ

“አርኖን” የወንዝ ስም ነው። ይህንን በዘዳግም 2፡24 ላይ እንዴት እንደተረጎምከው ተመልከት። (ስሞች እንዴት እንደሚተረጎሙ የሚለውን ተመልከት)

ለእኛ ከባድ የሆነ ከተማ አልነበረም

ይህ አሉታዊ አገላለጽ በጦርነት የነበራቸው ስኬት ላይ አጽንዖት ለመስጠት ጥቅም ላይ ውሏል። ይህ በአዎንታዊነት ሊነገር ይችላል። አ.ት፡ “ምንም እንኳን ከተማው ዙሪያው በረጃጅም ቅጥር የታጠረ ቢሆንም በየከተማው ያሉትን ሕዝቦች ማሸነፍ ችለናል። (ምጸት የሚለውን ተመልከት)

አልሄዳችሁም

ሙሴ እስራኤላውያኑን እንደ አንድ ሰው አድርጎ ይናገራል፣ ስለዚህ “አንተ” ነጠላ ቁጥር ነው። (See: Forms of You)

የያቦቅ ወንዝ

ይህ በሴዎን እና በአሞናውያን ምድር መካከል ድንበር ያበጀ ወንዝ ስም ነው። (ስሞች እንዴት እንደሚተረጎሙ የሚለውን ተመልከት)