am_tn/deu/01/09.md

1.3 KiB

በዚያን ጊዜ ነገርኳችሁ

እዚህ ጋ “እኔ” የሚያመለክተው ሙሴን ነው። “በዚያን ጊዜ” የሚለው ሐረግ እስራኤላውያን በኮሬብ፣ ይኸውም የሲና ተራራ ራሱ ነው፣ በዚያ የነበሩበትን ጊዜ ነው። አ.ት፡ “በኮሬብ በነበርንበት ጊዜ ነገርኳችሁ” (See: Assumed Knowledge and Implicit Information)

ለብቻዬ ልሸከማችሁ አልችልም

እዚህ ጋ “ልሸከማችሁ” ማለት “ልመራችሁ” ወይም “ላስተዳድራችሁ” ማለት ነው። አ.ት፡ “በራሴ ልመራችሁ ይከብደኛል” (የአነጋገር ዘይቤ የሚለውን ተመልከት)

እንደ ሰማይ ከዋክብት የበዛውን

ይህ ግነት ሲሆን ትርጉሙም እግዚአብሔር የእስራኤላውያንን ቁጥር እጅግ አብዝቶታል ማለት ነው። አ.ት፡ “እጅግ ብዙ ሕዝብ”(ግነት፣ ጥቅል አስተያየት እና Simile)

አንድ ሺህ ጊዜ

“አንድ ሺህ” የሚለው ሐረግ “በጣም ብዙ” የሚል ዘይቤአዊ አነጋገር ነው። አ.ት፡ “በጣም ብዙ ጊዜ” (ዘይቤአዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)

አንድ ሺህ

1000 (ቁጥሮች የሚለውን ተመልከት)