am_tn/2ch/30/10.md

2.3 KiB

የኤፍሬምና የምናሴ ክልሎች

ኤፍሬምና ምናሴ በእስራኤል ሰሜናዊ ክፍል ውስጥ የሚገኙ ሁለት ነገዶች ነበሩ። እዚህ ላይ “ኤፍሬም እና ምናሴ” የሚለው ሐረግ የሰሜናዊው እስራኤል አሥሩ ነገዶች አባላት የሆኑትን ሰዎች ሁሉ ያመለክታል፡፡ በ 2ኛ ዜና 30፡ 30 ውስጥ እንዴት እንደተረጎምከው ተመልከት ፡፡ ኣት: - “የሰሜናዊ የእስራኤል ነገዶች ግዛቶች” ( ሁሉን በአንዱ ወይም አንዱን በሁሉ መወከልን ፡ይመልከቱ)

እስከ ዛብሎን ድረስ

ዛብሎን በእስራኤል ሰሜን ጫፍ ውስጥ ከሚገኙት ነገዶች መካከል አንዱ ነበር ፣ ነገር ግን ከእነርሱ አልፈው ወደ ሰሜን ጥግ የሚደርሱ ሌሎች ሦስት ነገዶች ነበሩ።

የእግዚአብሔርም እጅ በይሁዳ ላይ ወረደ

እዚህ“የእግዚአብሔር እጅ” የሚለው የእርሱን አመራር የሚወክል ሲሆን ልክ በእጁ እየመራቸው ያለ ይመስላል። አት:- “እግዚአብሔር የይሁዳን ሕዝብ መራ።” ( ዘይቤያዊን ፡ይመልከቱ)

አንድ ልብ ለመስጠት

“አንድ ልብ” መኖሩ አንድነትን እና መስማማትን ያመለክታል ፡፡ ኣት: - “እንዲስማሙ ማድረግ” (ዘይቤያዊን ፡ይመልከቱ)

ትዕዛዙን እንዲያደርጉ

እዚህ “ትዕዛዙን ማድረግ” የሚለው አባባል የታዘዘውን ማድረግ የሚል ትርጉም አለው። ኣት: - “ትዕዛዙን መታዘዝ” (ፈሊጥን ፡ይመልከቱ)

በእግዚአብሔር ቃል የሆነውን የንጉሡንና የአለቆቹን ትዕዛዝ

“በእግዚአብሔር ቃል” የሚለው ሐረግ የሚያሳየው ንጉሡና መሪዎቹ ለእግዚአብሔር ቃል በመታዘዝ ትዕዛዙን እንደሰጡ ያሳያል ፡፡ ኣት: - “ንጉሡና መሪያዎቹ ለእግዚአብሔር ቃል በመታዘዝ የሰጧቸው ትእዛዝ” ወይም “እግዚአብሔር ከተናገረው ነገር የተነሳ ንጉሡና መኳንንቱ ያዘዙት”