2.2 KiB
2.2 KiB
በእግዚአብሔር ፊት ትክክል የሆነውን ነገር አደረገ
ዐይን ማየትን ይወክላል ፣ ማየት ደግሞ አመለካከትን ወይም ፍርድን ይወክላል። በ 2 ኛ ዜና 14፡ 2 ተመሳሳይ ሐረግ እንዴት እንደተረጎምክ ተመልከት ፡፡ አት: - “እግዚአብሔር ትክክል ነው ብሎ የሚወስነው” ወይም “እግዚአብሔር ትክክል ነው የሚለው” ( ዘይቤያዊን ፡ይመልከቱ)
በሁሉ የአባቱን የአሜስያስን ምሳሌ መከተል
ይህ የሚያመለክተው አባቱ በእግዚአብሔር ፊት ትክክል የሆነውን ነገር እንዳደረገ ነው ፡፡ ኣት: “አባቱ አሜስያስ እንዳደረገው” ( የሚጠበቅ እውቀትን እና ያልተገለጸ መረጃን ፡ይመልከቱ)
በሁሉም ነገር
ይህ ግርድፍ ነው ፡፡ ኣት: - “በተመሳሳይ መንገድ” ( ግነትን እና አጠቃላይን ፡ይመልከቱ)
እግዚአብሔርን ለመፈለግ ራሱን አዘጋጀ
እዚህ“ራሱን አዘጋጅ” አንድ ነገር ለማድረግ ቁርጥ ውሳኔ መወሰንን የሚያመለክት ነው ፡፡ እግዚአብሔርን መፈለግ እርሱን ለማወቅ ፣ ለማምለክ እና ለመታዘዝን መምረጥን ያመለክታል ፡፡ ኣት: - “እግዚአብሔርን ለመታዘዝ ቆርጦ ነበር” ( ዘይቤያዊን ፡ይመልከቱ)
በዘካርያስ ዘመን
እዚህ ላይ “የዘካርያስ ቀናት” ዘካርያስ ካህን የነበረበትን ዘመን የሚያመለክት አገላለጽ ነው ፡፡ አት: - “ዘካርያስ ካህን በነበረ ጊዜ” ( ዘይቤያዊን፡ይመልከቱ)
እግዚአብሔርን ይፈልግ በነበረ ጊዜ
“አግዚአብሔርን በፈለገበት ጊዜ ሁሉ”
እግዚአብሔርን ፈለገ
አግዚአብሔርን መፈለግ እርሱን ለማወቅ ፣ ለማምለክ እና ለመታዘዝ መምረጥን ያመለክታል ፡፡ ኣት: - “አግዚአብሔርን መታዘዝ መረጠ” ( ዘይቤያዊን ፡ይመልከቱ)