am_tn/2ch/22/01.md

1.6 KiB

የወንዶች ቡድን ... ታላላቅ ወንዶች ልጆችን ሁሉ ገድለዋቸዋል

ይህ የ 2ኛ ዜና መዋዕል 21፡ 16-17 ለተከሰቱ ክስተቶች ዳራዊ መረጃ ነው ፡፡ ቀደም ባለው ዘገባ ላይ አካዝያስ “ኢዮአስ” ተብሎ ተጠርቷል። ንጉሥ ሲሆን ስሙን ቀይሮ ሊሆን ይችላል ፡፡ ( ዳራዊ መረጃን ፡ይመልከቱ)

ታላላቅ ወንዶች ልጆቹ ሁሉ

“ሁሉም የኢዮራም ታላላቅ ልጆች”

ሃያ ሁለት ዓመት

“እድሜው 22 ዓመት ነበረ” ( ቁጥሮችን ፡ይመልከቱ)

ጎቶልያ

የአካዝያስ እናት ስም ይህ ነው። ( የስሞችን አተረጓጎም ፡ይመልከቱ)

እርሱ እንዲሁ በመንገዶቹ ሄደ

እዚህ “በመንገዶቹ ሄድ” የሚለው አባባል የአክዓብን ምሳሌ ይከተላል ማለት ነው ፡፡ ይህንን በ 2 ኛ ዜና 20፡32 ውስጥ እንዴት እንደተረጎምከው ተመልከት ፡፡ አት: - “እሱም ምሳሌውን ተከትሏል” ( ፈሊጥን ፡ይመልከቱ)

የአክዓብ ቤት

“ቤት” የሚለው ቃል በቤቱ ውስጥ የሚኖሩትን ቤተሰቦች የሚገልጽ ተተኪ ስም ነው ፡፡ በዚህ ሁኔታ ቤት የሚለው የአክአብን ዘር ያመለክታል ፡፡ በ 2 ኛ ዜና ምዕራፍ 21 6 ውስጥ ይህንን እንዴት እንደተረጊምከው ተመልከት ፡፡ ኣት: - “የአክዓብ ዘር” ( የባህሪ ስምን ፡ይመልከቱ)