am_tn/1sa/14/36.md

1.4 KiB

አጠቃለይ መረጃ

ሳኦል ከፍልስጥኤማውያን ጋር የነበረውን ጦርነት ለመቀጠል ፈልጓል፡፡

ከመካከላቸው አንድ እንኳ በሕይወት እንዲኖር አንተው

ለግድያው አጽንዖት ለመስጠት ይህ በአሉታዊ መንገድ ተገልጾአል፡፡ በአዎንታዊ መልኩም ሊገለጽ ይችላል፡፡ አት፡- "እያንዳንዳቸውን እንግደል' (ምጸት ተመልከት)

ደስ የሚያሰኝህን ሁሉ አድርግ

ጦርነቱን ለመቀጠል ሳኦል የሠራዊቱን ድጋፍ አግኝቶአል፡፡

ወደ እግዚአብሔር እንቅረብ

በዚህ ስፍራ "ወደ እግዚአብሔር መቅረብ' እርሱን ምክር ከመጠየቅ ጋር ተያይዟል፡፡ አት፡- "ምን ማደረግ እንዳለብን እግዚአብሔርን እንጠይቅ' (ምትክ ቃል ተመልከት)

በእስራኤል እጅ አሳልፈህ ትሰጣቸዋለህን?

በዚህ ስፍራ "እጅ' እነርሱን ለማሸነፍ የሚሆንን ኃይል ያመለክታል፡፡ አት፡-"እንድናሸንፋቸው አስችለን' (ምትክ ቃል ተመልከት)

በዚያን ቀን ግን እግዚአብሔር አልመለሰለትም

ይህ እግዚአብሔር ሳኦልን ለመርዳት ፈቃደኛ እንዳልሆነ ያመላክታል፡፡