am_tn/1sa/12/16.md

1.1 KiB

በዓይኖቻችሁ ፊት

በዚህ ስፍራ "ዓይኖች' የሚለው ቃል የእስራኤልን ሕዝብ ይወክላል፡፡ አት፡- "የእስራኤል ሕዝብ ሁሉ ሊያይ በሚችልበት ግልጽ ስፍራ' (ተለዋጭ ቃል ተመልከት)

የስንዴ መከር ዛሬ አይደለምን?

ሳሙኤል የመከር ጊዜ እንደሆነ ያውቃል፡፡ በአብዛኛው በዚህ ጊዜ ዝናብ እንደማይዘንብ ስለዚህ የእግዚአብሔር ፍርድ በመሆኑ ዝናቡ መከራቸውን እንደሚያጠፋ ሕዝቡ እንዲያውቅ አጽንዖት ለመስጠት አሳብ ገላጭ ጥያቄ ይጠቀማል፡፡ አት፡- "የመከር ጊዜ ነው በአብዛኛውም በዚህ ጊዜ አይዘንብም' (አሳብ ገላጭ ጥያቄ ተመልከት)

ነጎድጓድና ዝናብ ይልካል

ሳሙኤል በመከር ጊዜ እህሉን የሚያጠፋ ከባድ ዝናብ በመላክ ንጉስ ስለመጠየቃቸው እግዚአብሔር እሥራኤልን እንዲቀጣ ይጠይቃል፡፡