am_tn/1sa/10/11.md

1.9 KiB

የቂስን ልጅ ያገኘው ምንድን ነው

ሊሆኑ የሚችሉ ትርጉሞች፡- 1) ሕዝቡ መረጃ እየጠየቀ ነው 2) ሳኦል አስፈላጊ ሰው አይደለም የሚል ትርጉም ያለው አሳብ ገላጭ ጥያቄ ነው፡፡ አት፡- "ቂስ አስፈላጊ ሰው አይደለም፣ ልጁ ነቢይ ሆነ የሚለው እውነት ሊሆን አይችልም፡፡' (አሳብ ገላጭ ጥያቄ ተመልከት)

የቂስ ልጅ

"ሳኦል የቂስ ልጅ'

አባታቸውስ ማን ነው

ይህ ሰው፣ ነቢይ መሆን የአንድ ሰው ወላጆች እነማን ከመሆናቸው ጋር የሚያያዝው ምንም ነገር እንደሌለ ሕዝቡን ለማሳሳብ አሳብ ገላጭ ጥያቄ ይጠቀማል፡፡ ይህ ጥያቄ በገላጭ አባባል ሊገለጽ ይችላል፡፡ አት፡- "የእነዚህ የሌሎቹ ነቢያት ወላጆች እነማን መሆናቸው አስፈላጊ ነገር አይደለም፡፡ ቁም ነገሩ፣ በሚያስገርም ሁኔታ፣ ሳኦል የእግዚአብሔርን መልእክት መናገሩ ነው፡፡' (አሳብ ገላጭ ጥያቄዎች ተመልከት)

ስለዚህም፡- "ሳኦል ደግሞ ከነቢያት ወገን ነውን?' የሚል አባባል ሆነ

ይህ በእስራኤላውያን መካከል ምሳሌ ሆነ፡፡ አንድ ሰው ከዚያ በፊት አድርጎት የማያውቀውን ነገር ሳይታሰብ አድርጉት ሲገኝ አድናቆትን ለመግለጽ ሰዎች በግልጽ ይህን ይላሉ፡፡ አት፡- "ሰዎች አንዳንድ ዘገባዎችን ማመን ባቃታቸው ጊዜ፣ ከዚያም የተነሳ፣ ለሳኦል ስለሆነው አሰቡና እንዲህ አሉ፣ ‘በውኑ ሳኦል ከነቢያት አንዱ ነውን?'' (ምሳሌዎችንና እንደሚታወቅ ታሳቢ የተደረገ እውቀትና ግልጽ ያልተደረገ መረጃ ተመልከት)