ለሰውዬው ምን እናመጣለታለን
ሥጦታ መሥጠት ለእግዚአብሔር ሰው የአክብሮት ምልክት ነው፡፡
የእግዚአብሔር ሰው
ይህ ሐረግ በአብዛኛው የእግዚአብሔር ነቢይ ማለት ነው፡፡ ይህንን በ1ሳሙኤል 2፡27 እንዴት እንደተረጎምህ ተመልከት፡፡ አት፡- "ከእግዚአብሔር ቃል ሰምቶ የሚናገር ሰው'
የሰቅል ሩብ
"የሰቅል አንድ አራተኛ'፡፡ ሰቅል በብሉይ ኪዳን አገልግሎት ይሰጥ የነበረ የገንዘብ ዓይነት ነው፡፡ (የመጽሐፍ ቅዱስ ገንዘቦችና ክፍልፋዮች ተመልከት)