am_tn/1sa/05/01.md

1.1 KiB

አሁን

ቃሉ የታሪኩ አዲስ ክፍል መጀመሩን ያሳያል፡፡ ቋንቋህ ተመሳሳይ ትርጉም የሚሰጥ ቃል ወይም ሐረግ ካለ በዚህ ስፍራ ልትጠቀም ትችላለህ፡፡

የእግዚአብሔር ታቦት

ይህንን በ1ሳሙኤል 3፡3 እንዴት እንደተረጎምህ ተመልከት፡፡ ይህ በ1ሳሙኤል 4፡3-4 "የእግዚአብሔር የኪዳኑ ታቦት' ከሚለው ጋር ተመሳሳይ ነው፡፡

የዳጎን ቤት

ይህ የፍልስጥኤማውያንን አምላክ የዳጎንን ቤተ ጣዖት የሚያመለክት ነው፡፡

እነሆም ዳጎን

"ዳጎንን ለማየት እጅግ በአድናቆት ነበሩ'

ዳጎን በምድር ላይ በግምባሩ ወድቆ ነበር

እግዚአብሔር በሌሊት ሐውልቱ በግምባሩ እንዲወድቅ እንዳደረገ አንባቢው ማስተዋል አለበት፡፡ (እንደሚታወቅ ታሳቢ የተደረገ እውቀትና ግልጽ ያልተደረገ መረጃ ተመልከት)