am_tn/1sa/04/07.md

2.4 KiB

አሉ … አሉ

"ለራሳቸው አሉ … ለእርስ በእርሳቸው አሉ' ወይም "ለእርስ በእርሳቸው አሉ … ለእርስ በእርሳቸው አሉ'ሁለተኛው ሐረግ ፍልስጥኤማውያን ለርስ በርሳቸው ያሉትን በግልጽ ያመለክታል፡፡ የመጀመሪያው ሐረግ ግን ወይ ያሰበቱን ወይም ለእርስ በእርሳቸው ያሉትን ሊያመለክት ይችላል፡፡ ከተቻለ ለማን እንደተነገረ አታመልክት፡፡

እግዚአብሔር መጥቶአል

ፍልስጥኤማውያን በብዙ አማልክት ያመልካሉ፣ ስለዚህ ከእነዚያ አማልክት መካከል አንዱ ወይም የማያመልኩት አንዱ ወደ ሰፈር እንደመጣ አምነዋል፡፡ ሌላኛው ሊሆን የሚችለው ትርጉም "ያህዌ መጥቶአል' ሲሉ የእስራኤልን አምላክ መደበኛ ስም እየጠሩ ነበር የሚለው ነው፡፡ ምክንያቱም 4፡8 ስለ "አማልክት' ይናገራል፣ አንዳንድ ትርጉሞች "እግዚአብሔሮች መጥተዋል' ይላሉ፣ ይኄውም፣ "አማልክት መጥተዋል' ማለት ነው፡፡ (ተውላጠ ስሞች ተመልከት)

ከእነዚህ ኃያላን አማልክት እጅ ማን ያድነናል?

ይህ አሳብ ገላጭ ጥያቄ ጥልቅ ፍርሃት መግለጫ ነው፡፡ በገላጭ አባባል ሊጻፍ ይችላል፡፡ አት፡- "ከእነዚአህ ኃያላን አማልክት እጅ ሊያድነን የሚችል ማንም የለም፡፡' (አሳብ ገላጭ ጥያቄዎች ተመልከት)

እነዚህ አማልክት …የመቱ አማልክት

ምክንያቱም በቁጥር 7 አምላክ (ወይም እግዚአብሔር) የሚለው ቃል በነጠላ ቁጥር ነው፣ ሊሆኑ ከሚችሉ ብዙ አማልክት መካከል አንዳቸውን ወይም የእስራኤልን አምላክ መደበኛ ስም በመጠቀም "ይህ ኃያል እግዚአብሔር … የመታ እግዚአብሔር' በሚያመለክት መልኩ በርካታ ትርጉሞች "ይህ ኃያል አምላክ … የመታ አምላክ' ይላሉ፡፡ (ተውላጠ ስሞች ተመልከት)

ሰዎች ሁኑ

ይህ ፈሊጣዊ ንግግር ነው፡፡ አት፡- "ብርቱዎች ሁኑ ተዋጉ' (ፈሊጣዊ ንግግር ተመልከት)