am_tn/1sa/02/09.md

1.7 KiB

አያያዥ አሳብ

ሐና ለእግዚአብሔር መዘመሯን ቀጥላለች፡፡ (አጓዳኝነት ተመልከት)

የታማኞቹን ሰዎች እግር ይጠብቃል

በዚህ ስፍራ "እግር' የሚለው ስም አንድ ሰው ለሚሄድበት መንገድ ጥቅም ላይ የሚውል ስዕላዊ ንግግር ነው፣ በሌላ በኩል ደግሞ አንድ ሰው ሕይወቱን ለመኖር የወሰነበትን መንገድ የሚያመለክት ዘይቤአዊ ንግግር ነው፡፡ አት፡- "የተሳሳተ ውሳኔ እንዳይወስኑ ታማኞቹን ይጠብቃል' ወይም "ታማኞቹን ሰዎች ተገቢ ውሳኔ እንዲወስኑ ያስችላቸዋል፡፡' (ስዕላዊና ዘይቤአዊ ንግግር ተመልከት)

ኃጢአን ግን ዝም ብለው በጨለማ ይቀመጣሉ

በአድራጊ ማሰሪያ አንቀጽ እግዚአብሔር ኃጢአተኛውን ይገድላል በሚል ሊገለጽ የሚችለው የተነገረበት የአክብሮት መንገድ ነው፡፡ አት "እግዚአብሔር ኃጢአተኛውን በጨለማ ዝምታ ውስጥ ያስቀምጣል' ወይም "እግዚአብሔር ኃጢአተኛውን በጨለማና በሙታን የዝምታ ዓለም ውስጥ ያስቀምጣል' (የማያስደስትን ቃል በሌላ ቃል መጠቀም ተመልከት)

ኃጢአን በዝምታ እንዲቀመጡ ይደረጋሉ

"በዝምታ እንዲቀመጡ ይደረጋሉ' የሚሉት ቃላት "ዝም እንዲሉ ይደረጋሉ' ለሚለው ፈሊጣዊ ንግግር ናቸው፡፡ (ፈሊጣዊ ንግግር እና አድራጊና ተደረጊ ማሰሪያ አንቀጽ ተመልከት)

በኃይሉ

"ኃይለኛ ከመሆኑ የተነሳ'