am_tn/1sa/01/11.md

1.1 KiB

አያያዥ አሳብ

ሐና ወደ እግዚአብሔር የምታደርገው ጸሎት ቀጠለ፡፡

የባርያህን መከራ

መከራ የሚለው የነገር ስም በማሰሪያ አንቀጽ ሐረግነት ሊተረጎም ይችላል፡፡ ይህ የሚከተሉትን ሊያመለክት ይችላል፡- 1) የሐናን ማርገዝ አለመቻል፡፡ አት፡- "ማርገዝ ካለመቻሌ የተነሣ ምን ያህል መከራ እየተቀልኩ ነው' ወይም 2) ፍናን እርሷን ሁል ጊዜ የምታዋርድበትን መንገድ፡፡ አት፡- "ያቺ ሴት ምን ያህል መከራ እያሳየችኝ አንደሆነ' (የነገር ስሞች ተመልከት)

አስበኝ

እግዚአብሔር ስለ ሐና እርምጃ እንዲወስድ የቀረበ የተለየ ልመና ነው፡፡ ሐና ላይ ምን እየሆነባት እንዳለ እግዚአብሔረ ያውቃል፣ አልረሳም፡፡

ባርያህን አትርሳ

ይህ ሐረግ የሚለው ነገር "አስበኝ' ከሚለው ጋር ተመሣሣይ ነው ማለት ይቻላል፡፡ (አጓዳኝነት ተመልከት)