am_tn/1sa/01/09.md

1.7 KiB

አጠቃላይ መረጃ

ሐና ወደ እግዚአብሔር መጸለይ ጀመረች ዔሊም ተመለከታት፡፡

በኋላም ሐና ተነሣች

ግልጽ ያልሆነ መረጃ በዚህ ስፍራ ግልጽ ሊደረግ ይችላል፡፡ ወይ የሐና ድንኳን ከመገናኛው ድንኳን ቀጥሎ ነበር ወይም ለመጸለይ ከድንኳንዋ ወደ መገናኛው ድንኳን ሄዳ ነበር፡፡ አት፡- "በኋላም ሐና ተነሣች ለመጸለይም ወደ እግዚአብሔር ቤት ሄደች፡፡' (እንደሚታወቅ ታሳቢ የተደረገ እውቀትና ግልጽ ይልተደረገ መረጃ ተመልከት)

ካህኑም ዔሊ

"ም' የሚለው ቃል እየተተረከ የዋናው ታሪክ ፍሰት መቋረጡን ለማመልከት ጥቅም ላይ ውሏል፡፡ በዚህ ስፍራ ጸሐፊው በታሪኩ ስለሌላ አንድ ሰው ይነግረናል፡፡ ይህም ሰው ካህኑ ዔሊ ነው፡፡ (የስሞች አተረጓገም መንገድ፡- ተመልከት)

የእግዚአብሔር መቅደስ

"መቅደሱ' በእርግጥ ድነኳን ነበር ነገር ግን ሕዝቡ ያመልክበት የነበረ ስፍራ ስለ ነበር፣ በዚህ ስፍራ መቅደስ ብሎ መተረጎም ይበልጥ የተመረጠ ነው፡፡

በልባዋ ትመረር ነበር

ምንም ልጆች ስለሌላትና የባሏ ሌላኛዋ ሚስቱ ፍናና ያለማቋረጥ ታዋርዳት ስለነበር ሐና እጅግ ትታወክና ታዝን ነበር፡፡ (እንደሚታወቅ ታሳቢ የተደረገ እውቀትንና ያልተገለጸ መረጃን ተመልከት)