am_tn/1ch/19/16.md

2.0 KiB

አጠቃላይ መረጃ

በ 1ኛ ዜና 19 ፡15 ላይ ከኢዮአብ ሸሽተው የመጡ ሶርያውያን በሌሎች ሶርያውያን ተጠናክረው እስራኤልን እንደገና እንደወጉ ቁጥር 16-19 ይናገራል ፡፡

ሶርያውያንም አይተዋል

ሶርያውያኑ የተገነዘቡት እንዳዩት ይነገራል። አት: - “ሶርያውያን ተረድተው ነበር” (የባህሪ ስምን ፡ ይመልከቱ)

ለማጠናከሪያነት ተልኳል

“ተጨማሪ ወታደሮችን ጠይቀዋል”

ሾፋክ…አድርአዛር

እነዚህ የሰዎች ስሞች ናቸው ፡፡ ( ስሞችን እንዴት እንደሚተረጉሙ ፡ይመልከቱ)

ዳዊትም ይህ ሲነገረው

ይህ በገቢራዊ ቅርፅ ሊገለፅ ይችላል ፡፡ ኣት: የዳዊት መልእክተኞች ብዙ የሶርያ ሠራዊት እየመጣ መሆኑን በነገሩት ጊዜ ( ገቢራዊን ወይም ተብሮአዊን ፡ይመልከቱ)

እርሱ ሰብስቦ ... አስተካከለ

ዳዊት እነዚህን ነገሮች ብቻውን አላደረገም። የእርሱም ሆነ የአገሬው ሰዎች ረድተውታል። ኣት: “ዳዊትና አገልጋዮቹ ተሰበሰቡ… ዳዊትና አገልጋዮቹም አደራጁ” (ሁሉን በአንዱ ወይም አንዱን በሁሉ መወከልን፡ ይመልከቱ)

እስራኤል ሁሉ

ይህ አጠቃላይ ነው ፡፡ የእስራኤል ህዝብ በሙሉ ወደ ውጊያው አልመጡም ፡፡ ኣት: - “እጅግ ብዙ ቁጥር ያላቸው እስራኤላውያን” (ግነትን እና አጠቃላይን ፡ ይመልከቱ)

ዝግጅት አደረገ

“አደራጀ”

ተዋጉ

እዚህ “እርሱ” የሚለው ቃል ከዳዊት በተጨማሪ የዳዊትን ወታደሮች ያመለከታል ፡፡ ኣት: - “ሶርያውያን ዳዊትንና ወታደሮቹን ተዋጉ” ( ሁሉን በአንዱ መወከልን ፡ ይመልከቱ)