209 lines
20 KiB
Plaintext
209 lines
20 KiB
Plaintext
\id 1JN
|
|
\ide UTF-8
|
|
\h 1ኛ ዬሐንስ
|
|
\toc1 1ኛ ዬሐንስ
|
|
\toc2 1ኛ ዬሐንስ
|
|
\toc3 1jn
|
|
\mt 1ኛ ዬሐንስ
|
|
|
|
\s5
|
|
\c 1
|
|
\cl ምዕራፍ 1
|
|
\p
|
|
\v 1 ከመጀመሪያው ስለ ነበረው፣ ስለ ሰማነው፣ በዓይኖቻች ስላየነው፣ ስለ ተመለከትነው ፣በእጆቻችንም ስለ ዳሰስነው ስለ ህይወት ቃል
|
|
\v 2 ህይወትም ተገልጦ ነበር ፤እኛም አይተናል፣ምስክሮችም ነን፤ በአብ ዘንድ ስለ ነበረው ለእኛም ስለ ተገለጠው፣ የዘላለም ሕይወት እንናገራለን፤
|
|
|
|
\s5
|
|
\v 3 ከእኛም ጋር ህብረት እንዲኖራቸሁ፣ ያየነውንና የሰማነውን እንነግራችኋለን፤ ህብረታችንም ከአብና፣ ከልጁ ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር ነው፡፡
|
|
\v 4 ደስታችሁም ሙሉ እንዲሆን ፣እነዚህን ነገሮች እንጽፍላችኋለን።
|
|
|
|
\s5
|
|
\v 5 ከእርሱ የሰማነው፣ለናንተም የምንነግራችሁ መልዕክት፣ እግዚአብሔር ብርሃን ነው፤ በእርሱም ምንም ጨለማ የለም፤ የሚል ነው፡፡
|
|
\v 6 ከእርሱ ጋር ህብረት አለን እያልን፣ ነገር ግን በጨለማ ውስጥ ብንመላለስ፣እንዋሻለን ፣እውነትንም አናደርግም፡፡
|
|
\v 7 እርሱ ብርሃን እንደሆነ ፣ በብርሃን ብንመለላለስ እርስ በርሳችን ህብረት ይኖረናል፡፡የልጁ የኢየሱስ ክርስቶስም ደም ከሃጢአት ሁሉ ያነጻናል።
|
|
|
|
\s5
|
|
\v 8 ሃጢያት የለብንም ብንል፣ ራሳችንን እናስታለን፣ እውነትም በእኛ ውስጥ የለም።
|
|
\v 9 ነገር ግን ሃጢያታችንን ብንናዘዝ፣ሃጢያታችንን ይቅር ሊለንና ከዓመጽ ሁሉ ሊያነጻን፣ የታመነና ፃድቅ ነው፡፡
|
|
\v 10 ሃጢአት አላደረግንም ብንል፣ ሃሰተኛ እናደርገዋለን፣ ቃሉም በእኛ ውስጥ የለም፡፡
|
|
|
|
\s5
|
|
\c 2
|
|
\cl ምዕራፍ 2
|
|
\p
|
|
\v 1 የተወደዳችሁ ልጆቼ ፣ሃጢያት እንዳታደርጉ ይህን እፅፍላችኋላሁ። ግን ማንም ሃጢያት ቢያደርግ ፣ ከአብ ዘንድ ጠበቃ አለን ፤እርሱም ፃድቅ የሆነ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው ፡፡
|
|
\v 2 እርሱ የእኛ ብቻ ሳይሆን፣ የዓለሙም ሁሉ ሃጢዓት ማስተስረያ ነው፣፡፡
|
|
\v 3 ትዕእዛዙን የምንጠብቅ ከሆነ ፣በዚህ እርሱን እንዳወቅነው እናውቃለን።
|
|
|
|
\s5
|
|
\v 4 "እግዚአብሔርን አውቀዋለሁ" የሚል ፣ግን ትዕዛዛቱን የማይጠብቅ፣ ውሸታም ነው ፣እውነትም በውስጡ የለም፡፡
|
|
\v 5 ሆኖም ማንም ቃሉን ቢጠብቅ፣ በርግርጥ በዚያ ሰው ለእግዚአብሔር ያለው ፍቅር ተገልጧል፤ በዚህም በእርሱ እንደሆንን እናውቃለን።
|
|
\v 6 በእግዚአብሔር እኖራለሁ የሚል ፣ኢየሱስ ክርስቶስ እንደኖረ መኖር አለበት።
|
|
|
|
\s5
|
|
\v 7 የተወደዳችሁ፣የምጽፍላችሁ በመጀመሪያ የነበረውን አሮጌ ትዕዛዝ እንጂ አዲስ ትዕዛዝ አይደለም።አሮጌውም ትእዛዝ የሰማችሁት ቃል ነው፡፡
|
|
\v 8 ሆኖ በክርስቶስና በናንተ እውነት የሆነውን አዲሱን ትእዛዝ እጽፍላችኋለሁ።ምክንያቱም ጨለማው አልፎ እውነተኛው ብርሃን እያበራ ነው።
|
|
|
|
\s5
|
|
\v 9 በብርሃን አለሁ እያለ ፣ወንድሙን ግን የሚጠላ ፣አሁንም እንኳ በጨለማ ውስጥ ነው፡፡
|
|
\v 10 ወንድሙን የሚወድ በብርሃን ይኖራል። የሚያሰናክል ሁኔታም የለም፡፡
|
|
\v 11 ወንድሙን የሚጠላ በጨለማ ውስጥ ነው፣ በጨለማም ይኖራል፤ ወዴት እንደሚሄድም አያውቅም ፣ምክንያቱም ጨለማው ዓይኖች አሳውሮታል፡፡
|
|
|
|
\s5
|
|
\v 12 ልጆች ሆይ! ኃጢያታችሁ በክርስቶስ ስም ይቅር ስለተባለ እፅፍላችኋለሁ፡፡
|
|
\v 13 አባቶች ሆይ! ከመጀመሪያ የነበረውን አውቃኋልና እጽፍላችኋለሁ። ወጣቶች ሆይ! ክፉውን ስላሸነፋችሁ እጽፍላችኋለሁ፡፡ ታናናሽ ልጆች ሆይ! አብን ስላወቃችሁ እጽፍላችኋለሁ፡፡
|
|
\v 14 አባቶችሆይ! ከመጀመሪያ የነበረውን አውቃችኋልና እጽፍላችኋለሁ። ወጣቶች ሆይ! ብርቱዎች ስለሆናቹ ፣የእግዚአብሔርም ቃል በእናንተ ስለሚኖር፣ ክፉውንም አሸንፋችኋልና እጽፍላችኋለሁ፡፡
|
|
|
|
\s5
|
|
\v 15 ዓለምን ወይም በዓለም ያሉት ነገሮች አትውደዱ። ማንም ዓለምን ቢወድ የአብ ፍቅር በርሱ ውስጥ የለም፡፡
|
|
\v 16 በዓለም ያለው ሁሉ፣ የሥጋ ምኞት፣ የዓይን አምሮትና ትምክህት ከዓለም እንጂ ከአብ አይደሉም፡፡
|
|
\v 17 ዓለሙና ምኞቱም ያልፋሉ፣የእግዚአብሔርን ፈቃድ የሚያደርግ ግን ለዘላለም ይኖራል፡፡
|
|
|
|
\s5
|
|
\v 18 ታናናሾች ልጆች ሆይ! የክርስቶስ ተቀዋሚ ስለመምጣቱ እንደሰማችሁት ፣ይህ የመጨረሻው ሰዓት ነው፡፡ አሁንም እንኳ፣ ብዙ የክርስቶስ ተቃዋሚዎች መጥተዋል፡፡
|
|
\v 19 ከእኛው መካከል ወጥተዋል ፣ከእኛ ወገን ግን አልነበሩም። ከእኛ ወገን ቢሆኑ ኖሮ፣ ከእኛ ጋር ፀንተው ይኖሩ ነበር። ሆኖም ከእኛ ወገን እንዳልነበሩ እንዲገለጥ ወጡ።
|
|
|
|
\s5
|
|
\v 20 እናንት ግን፣ከቅዱሱ የተቀበላችሁት ቅባት ስላላችሁ፣ሁላችሁም እውነትን ታውቃላችሁ።
|
|
\v 21 የምጽፍላችሁ እውነትን ስለማታውቁ አይደለም፤ነገር ግን ስለምታውቁትና፣ በእውነትም ምንም ሃሰት ስለሌለ ነው።
|
|
|
|
\s5
|
|
\v 22 ኢየሱስ ክርስቶስ መሆኑን ከሚክድ በስተቀር ሃሰተኛ ማነው ነው? አብና ወልድን ስለሚክድ፣እንዲህ ዓይነት ሰው የክርስቶስ ተቃዋሚ ነው።
|
|
\v 23 ወልድን የሚክድ ሁሉ አብ የለውም፤ ወልድንን የሚያውቅ አብም ደግሞ አለው።
|
|
|
|
\s5
|
|
\v 24 እናንተ ግን ፣ከመጀመሪያው የሰማችሁት በውስጣችሁ ይኑር። ከመጀመሪያ የሰማችሁት፣በእናንተ ቢኖር፣እናንተም በወልድና በአብ ትኖራላችሁ።
|
|
\v 25 እርሱ የሰጠን ተስፋ ይህ ነው፤ እርሱም የዘላለም ሕይወት ነው።
|
|
\v 26 የሚያስቷችሁን በተመለከተ ፣ ይህን ፅፌላችኋለሁ፡፡
|
|
|
|
\s5
|
|
\v 27 እናንተ ግን የተቀበለች ቅባት በእናንተ ስለሚኖር ፣ማንም እንዲያስተምራችሁ አያስፈልጋችሁም። የርሱም ቅባት ስለ ሁሉም ነገሮች እውነት እንጂ ሃሰት ስለማያስተምራችሁ ፣ እንደተማራችሁት በርሱ ኑሩ፡፡
|
|
\v 28 አሁንም የተወዳዳችሁ ልጆች፣ በሚገለጥበለት ጊዜ ድፍረት እንዲኖረንና ፣በመምጣቱም እንዳናፍር በእርሱ ኑሩ፡፡
|
|
\v 29 እርሱ ፃድቅ እንደሆነ ካወቃችሁ ፣ፅድቅን የሚያደርግ ሁሉ ከርሱ እንደተወለደ ታውቃላችሁ፡፡
|
|
|
|
\s5
|
|
\c 3
|
|
\cl ምዕራፍ 3
|
|
\p
|
|
\v 1 የእግዚአብሔር ልጆች ተብለን እንድንጠራ፣አብ የሰጠን ፍቅር ፣ምን ዓይነት እንደሆነ አስተውሉ ፤ እኛም ልክ እንደዛው ነን! በዚህ ምክንያት ዓለም እርሱን እንደማያውቀው እኛንም አያውቀንም።
|
|
\v 2 የተወደዳችሁ፣አሁን የእግዚአብሔር ልጆች ነን፤ ምን እንደምንሆን ገና አልተገለጠም። ክርስቶስ በሚገለጥበት ጊዜ እርሱን እንደምንመስል እናውቃለን፤ምክንያቱም ትክክለኛ ማንንነቱን እናየዋለን።
|
|
\v 3 በእርሱም ላይ ይህ ጽኑ እምነት ያለው ሁሉ፣ እርሱ ንፁህ እንደሆነ ራሱን ያነፃል፡፡
|
|
|
|
\s5
|
|
\v 4 ኃጢያትን የሚሠራ ሁሉ ዐመጽን ያደርጋል፣ ኃጢአትም ዐመጽ ነው፡፡
|
|
\v 5 ኃጢያትን ለማስወገድ ክርስቶስ እንደተገለፀ ታውቃላችሁ፣ በእርሱም ኃጢያት የለም፡፡
|
|
\v 6 በእርሱ የሚኖር ኃጢያት አያደርግም፡፡ ኃጢያት የሚያደርግ እርሱን አላየውም ወይም አላወቀውም፡፡
|
|
|
|
\s5
|
|
\v 7 የተወደዳችሁ ልጆች፣ ማንም አያስታችሁ፡፡ ክርስቶስ ፃድቅ እንደሆነ ሁሉ፣ ፅድቅን የሚያደርግ ፃድቅ ነው።
|
|
\v 8 ኃጢያት የሚያደርግ ከዲያብሎስ ነው፤ምክንያቱም ዲያብሎስ ከመጀመሪያው ኃጢያት አድርጓል፡፡ በዚህም ምንክያት የዲያብሎስን ሥራ ለማፍረስ ፣የእግዚአብሔር ልጅ ተገልጧል፡፡
|
|
|
|
\s5
|
|
\v 9 የእግዚአብሔር ዘር በርሱ ስለሚኖር ፣ከእግዚአብሔር የተወለደ ሁሉ ኃጢያትን አያደርግም፤ ከእግዚአብሔር ተወልዷልና ኃጢያትን ሊያደርግም አይችልም።
|
|
\v 10 በዚህም የእግዚአብሔር ልጆችና የዲያብሎስ ልጆች ይታወቃሉ፡፡ ፅድቅን የማያደርግ ወይም ወንድሙን የማይወድ ሁሉ ከእግዚአብሔር አይደለም፡፡
|
|
|
|
\s5
|
|
\v 11 ከመጀመሪያው የሰማችኋት መልእክት፣ይህ እርስ በርሳችን እንድንዋደድ የሚለው ነው።
|
|
\v 12 ክፉ እንደሆነውና ወንድሙን እንደ ገደለው እንደ ቃየል አይደለም። የገደለው ለምንድን ነው? ምክንያቱ የራሱ ሥራ ክፉ፣ የወንድሙ ጽድቅ ስለነበረ ነው፡፡
|
|
|
|
\s5
|
|
\v 13 ወንድሞች፣ ዓለም ቢጠላችሁ፣አትደነቁ።
|
|
\v 14 ወንድሞችን ስለምንወድ ፣ከሞት ወደ ህይወት እንደተሻገርን እናውቃለን። ፍቅር የሌለው በሞት ውስጥ ይኖራል፡፡
|
|
\v 15 ወንድሙን የሚጠላ ነፍሰ ገዳይ ነው፡፡ ነፍሰ ገዳይ የሆነ ሁሉ፣ በውስጡ የዘላለም ህይወት እንደሌለው ታውቃላችሁ፡፡
|
|
|
|
\s5
|
|
\v 16 ክርስቶስ ለእኛ ህይወቱን ሰጥቷልና፣በዚህ ፍቅርን እናውቃለን።እኛም ለወንድሞቻችን ህይወታችንን አሳልፈን መስጠት ይገባናል።
|
|
\v 17 ነገር ግን ማንም የዚህ ዓለም ንብረት ያለውና፣ወንድሙም የሚያስፈልገውን አውቆ፣ባይራራለት፣ እንዴት የእግዚአብሔር ፍቅር በርሱ ይኖራል?
|
|
\v 18 የተወደዳችሁ ልጆቼ ፣በሥራና በእውነት እንጂ ፣በቃል ወይም በአንደበት አንዋደድ።
|
|
|
|
\s5
|
|
\v 19 በዚህም ከእውነት እንደሆንንና፣ልባችንም በፊቱ ትክክል እንደሆነ እናረጋግጣለን።
|
|
\v 20 ልባችን ግን የሚፈርድብን ከሆነ፣ እግዚአብሔር ከልባችን ይልቅ ታላቅ ነው፣ሁሉንም ያውቃል፡፡
|
|
\v 21 ወዳጆች ሆይ! ልባችን የማይፈርድብን ከሆነ፣በእግዚአብሔር ፊት ድፍረት አለን።
|
|
\v 22 ትዕዛዙን የምንጠብቅና፣በፊቱ ደስ የሚያሰኘውን የምናደርግ ስለሆነ፣ የምንለምነውንና ሁሉ እንቀበላለን፡፡
|
|
|
|
\s5
|
|
\v 23 የርሱም ትዕዛዙ፣በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም እንድናምንና፣ ትእዛዙን እንደሰጠን እንደዚያው እርስ በርስ እንድንዋደድ ነው፡፡
|
|
\v 24 የእግዚአብሔርን ትዕዛዝ የሚጠብቅ ፣በርሱ ይኖራል እግዚአብሔርም በርሱ ይኖራል፡፡በዚህም በሰጠን በመንፈሱ፣ በእኛ ውስጥ እንደሚኖር እናውቃለን።
|
|
|
|
\s5
|
|
\c 4
|
|
\cl ምዕራፍ 4
|
|
\p
|
|
\v 1 ወዳጆች ሆይ! መንፈስን ሁሉ አትመኑ፣ነገር ግን መናፍስት ከእግዚአብሔር መሆናቸውን መርምሩ፣ ምክንያቱም ብዙ ሃሰተኛ ነቢያት ወደ ዓለም ገብተዋል፡፡
|
|
\v 2 የእግዚአብሔርን መንፈስ በዚህ እናውቃለን፣- ጌታ ኢየሱስ በሥጋ እንደመጣ የሚቀበል መንፈስ ሁሉ ከእግዚአብሔር ነው።
|
|
\v 3 ኢየሱስን የማይቀበል መንፈስ ሁሉ ከእግዚአብሔር አይደለም። ይህ እንደሚመጣ የሰማችሁት የክርስቶስ ተቃዋሚው መንፈስ ነው፣ አሁን እንኳ በዓለም ውስጥ አለ፡፡
|
|
|
|
\s5
|
|
\v 4 የተወደዳችሁ ልጆች! እናንተ ከእግዚአብሔር ስለሆናችሁ፣ እነዚህን መናፍስት አሸንፋችኋል፣ ምክንያቱም በዓለም ካለው ይልቅ በእናንተ ያለው ይበልጣል፡፡
|
|
\v 5 እነዚህ መናፍስት ከዓለም ናቸው፣ስለሆነም የሚናገሩት ሁሉ የዓለምን ነው፣ዓለምም ይሰማቸዋል፡፡
|
|
\v 6 እኛ ከእግዚአብሔር ነን። እግዚአብሔርን የሚያውቅ ይሰማናል። ከእግዚአብሔር ያልሆነ ግን አይሰማንም። በዚህም የእውነት መንፈስንና ፣የስህተትን መንፈስን እናውቃለን፡፡
|
|
|
|
\s5
|
|
\v 7 ወዳጆች ሆይ! እርስ በርስ እንዋደድ፣ምክንያቱም ፍቅር ከእግዚአብሔር ነውና፣ ፍቅር ያለው ከእግዚአብሔር ተወልዷል፣ እግዚአብሔርንም ያውቃል፡፡
|
|
\v 8 ፍቅር የሌለው እግዚአብሔርን አያውቅም፣እግዚአብሔር ፍቅር ነውና፡፡
|
|
|
|
\s5
|
|
\v 9 በዚህ የእግዚአብሔር ፍቅር በመካከላችን ተገልጧል፣ እግዚአብሔር በርሱ እንድንኖር ፣አንድ ልጁን ወደ ዓለም ላከው፡፡
|
|
\v 10 ፍቅር እንደዚህ ነው፣እግዚአብሔርን ስለወደድነው ሳይሆን፣ እርሱ ስለወደደን ለኃጢያታችን ማስተሰረያ እንዲሆን ልጁን ላከ፡፡
|
|
|
|
\s5
|
|
\v 11 ወዳጆች ሆይ! እግዚአብሔር ይህን ያህል ከወደደን፣እኛም እርስ በርሳችን መዋደድ ይገባናል።
|
|
\v 12 ማንም እግዚአብሔርን አላየውም። እርስ በርሳችን ብንዋደድ፣ እግዚአብሔር በኛ ይኖራል፣ ፍቅሩም በእኛ ፍጹም ይሆናል፡፡
|
|
\v 13 መንፈሱን ሰጥቶናልና፣ በዚህም እኛ በእርሱ እንደምንኖር፣ እርሱም በኛ እንደሚኖር እናውቃለን።
|
|
\v 14 እኛም አይተናል፣እግዚአብሔር ልጁን የዓለም አዳኝ አድርጐ እንደላከውም እንመሰክራለን፡፡
|
|
|
|
\s5
|
|
\v 15 ማንም ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ ቢቀበል፣ እግዚአብሔር በርሱ ይኖራል ፤እርሱም በእግዚአብሔር ይኖራል፡፡
|
|
\v 16 እኛም እግዚአብሔር ለኛ ያለውን ፍቅር አውቀናል ደግሞም አምነናል። እግዚአብሔር ፍቅር ነው፣ በፍቅር የሚኖር በእግዚአብሔር ይኖራል፣እግዚአብሔርም በርሱ ይኖራል፡፡
|
|
|
|
\s5
|
|
\v 17 በፍርድ ቀን ድፍረት እንዲኖረን፣ይህም ፍቅር በመካከላችን ተፈጸሟል፣ እኛም በዚህ ዓለም እንደ እርሱ ነን ፡፡
|
|
\v 18 በፍቅር ፍርሃት የለም። ነገር ግን ፍጹም ፍቅር ፍርሃትን አውጥቶ ይጥላል፣ ምክንያቱም ፍርሃት የሚያመለክተው ቅጣት መኖሩን ነው። የሚፈራ ግን ፍቅሩ ፍፁም አይደለም፡፡
|
|
|
|
\s5
|
|
\v 19 አስቀድሞእግዚአብሔር ወዶናልና፣እኛም እንወደዋለን።
|
|
\v 20 አንድ ሰው "እግዚአብሔርን እወዳለሁ" እያለ ወንድሙን ግን ቢጠላ ሃሰተኛ ነው፤የሚያየውን ወንድሙን የማይወድ፣ የማያየውን እግዚአብሔርን ሊወድ አይችልም።
|
|
\v 21 እግዚአብሔርን የሚወድ ወንድሙን መውደድ አለበት፣የሚል ትእዛዝ ከእግዚአብሔር ተቀብለናል።
|
|
|
|
\s5
|
|
\c 5
|
|
\cl ምዕራፍ 5
|
|
\p
|
|
\v 1 ኢየሱስ ክርስቶስ እንደ ሆነ የሚያምን ሁሉ ከእግዚአብሔር ተወልዷል።አባት የሆነውን የሚወድ ሁሉ፣ከርሱ የተወለደውን ደግሞ ይወዳል።
|
|
\v 2 እግዚአብሔርን ስንወድና ትዕዛዙን ስንፈጽም፣ የእግዚአብሔርን ልጆች እንደምንወድ በዚህ እናውቃለን።
|
|
\v 3 እግዚአብሔርን የምንወደው የርሱን ትእዛዙን በመጠበቃችን ነው። የርሱም ትእዛዛት ከባዶች አይደሉም።
|
|
|
|
\s5
|
|
\v 4 ከእግዚአብሔር የተወለደ ሁሉ ዓለምን ያሸንፋል። ዓለምን የሚያሽንፈው እምነታችን ነው።
|
|
\v 5 ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ ከሚያምን በቀር፣ ዓለምን የሚየሸንፍ ማነው?
|
|
|
|
\s5
|
|
\v 6 በውሃና በደም የመጣው እርሱም ነው፣እርሱም ኢየሱስ ክርስቶስ፣ በውሃ ብቻ ሳይሆን፣ነገር ግን በውሃና በደም የመጣ ነው።
|
|
\v 7-8 የጥንቶችቹ የተሻሉት ቅጅዎች ይተውታል። ሦሶት ምስክሮች አሉ፤እነርሱም መንፈሱ ፣ውሃውና ደሙ ናቸው፤ሦስቱም በአንድ ይስማማሉ።
|
|
|
|
\s5
|
|
\v 9 የሰዎችን ምስክርነት የምንቀበል ከሆነ፣ የእግዚአብሔር ምስክርነት ደግሞ የበለጠ ነው። እግዚአብሔር ስለ ጁል የሰጠው ምስክር ይህ ነው።
|
|
\v 10 በእግዚአብሔር ልጅ የሚያምን በውስጡ ምስክር አለው። በእግዚአብሔር የማያምን ፣እግዚአብሔር ስለ ልጁ የመሰከረውን ምስክር ስለማያምን ሐሰተኛ አድርጎታል።
|
|
|
|
\s5
|
|
\v 11 ምስክሩም ይህ ነው ፣እግዚአብሔር የዘላለምን ህይወት እንደሰጥንና፣ይህም ህይወት በልጁ መሆኑ ነው።
|
|
\v 12 ልጁ ያለው ሕይወት አለው፥ የእግዚአብሔር ልጅ የሌለው ሕይወት የለውም።
|
|
|
|
\s5
|
|
\v 13 በእግዚአብሔር ልጅ ስም ለምታምኑ፣የዘላለም ህይወት እንዳላችሁ እንድታውቁ ፣እነዚህን ነገሮች እጽፍላችኋለሁ።
|
|
\v 14 በእርሱ ፊት ያለን ድፍረት ይህ ነው፣እንደ ፈቃዱ ማንኛውንም ነገር ብንጠይቀው፣ይሰማናል።
|
|
\v 15 የምንጠይቀውን ሁሉ እንደሚሰማን ካወቅን፣ከርሱ የጠየቅነውን ሁሉ እንደተቀበልን እናውቃለን።
|
|
|
|
\s5
|
|
\v 16 ማንም ወንድሙ ለሞት የማያበቃ ሃጢዓት ሲያደርግ ቢያይ፣ መጸለይ ይገባዋል፣ሞት የማይገባውን ሃጢዓት ለሚያደርጉት እግዚአብሔር ህይወትን ይሰጣል። ለሞት የሚያበቃ ኃጢዓት አለ። ያንን የተመለከተ ልመና እንዲያደርግ አላልኩም።
|
|
\v 17 ዓመጽ ሁሉ ኃጢዓት ነው፣ ነገር ግን ለሞት የማያበቃ ኃጢዓት አለ።
|
|
|
|
\s5
|
|
\v 18 ከእግዚአብሔር የተወለደ ሁሉ ኃጢዓት እንደማያደርግ እናውቃለን፣ከእግዚአብሔር የተወለደውን፣እግዚአብሔር ከክፉ ይጠብቀዋል ፣ክፉውም አይነካውም።
|
|
\v 19 እኛ ከእግዚአብሔር እንደሆንን፣ዓለም ሁሉ በክፉው ቁጥጥር ሥር እንደሆነ እናውቃለን።
|
|
|
|
\s5
|
|
\v 20 እኛ ግን የእግዚአብሔር ልጅ እንደመጣና እውነት የሆነውን እንድናውቅ ማስተዋል እንደሰጠን እናውቃለን፤ እኛም እውነት በሆነው በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ እንዳለን እናውቃለን። እርሱም እውነተኛ አምላክና የዘላለም ህይወት ነው።
|
|
\v 21 ልጆች ሆይ! ከጣዖታት ዓምልኮ ራሳችሁን ጠብቁ።
|