am_ulb/65-3JN.usfm

36 lines
2.8 KiB
Plaintext

\id 3JN
\ide UTF-8
\h 3ኛ ዮሐንስ
\toc1 3ኛ ዮሐንስ
\toc2 3ኛ ዮሐንስ
\toc3 3jn
\mt 3ኛ ዮሐንስ
\s5
\c 1
\cl ምዕራፍ 1
\p
\v 1 ሽማግሌው በእውነት ለምወደውና ለተወደደው ጋይዮስ።
\v 2 የተወደድክ ሆይ በነፍስህ እንደበለጸግህ በሁሉ ነገር እንድትበለጽግና በመልካም ጤንነት እንድትሆን እጸልያለሁ።
\v 3 ወንድሞች መጥተው በእውነት እንደምትሄድ ሲመሰክሩልኝ እጅግ ሀሴት አደረግሁኝ።
\v 4 ልጆቼ በእውነት መንገድ እየሄዱ እንደሆነ ከመስማት የበለጠ ደስታ የለኝም።
\s5
\v 5 የተወደድክ ሆይ ለወንድሞችም ሆነ ለእንግዶች በምታድርገው ነገር ስላለህ ታማኝነት
\v 6 ሁሉም በጉባኤ ፊት ይመሰክሩልሀል።ለእግዚአብሔር እንደሚገባ በጉዞአቸው በመደገፍህ መልካም አድርገሀል።
\v 7 ምክንያቱም ለተጠሩለት ስም አገልግሎት ሲወጡ ከአህዛብ ምንም አልወሰዱም።
\v 8 ስለዚህም የእውነት ማህበርተኞች እንሆን ዘንድ እንደነዚህ ያሉትን መርዳት ይገባናል።
\s5
\v 9 ስለአንድ ጉዳይ ለቤተክርስቲያን ጽፌ ነበር ነገር ግን በመካከላቸውአለቃ ሊሆን የሚወደው ዲዮትሪፈስ አይቀበለንም።
\v 10 ስለዚህ በምመጣበት ጊዜ ያደረገውን ነገርና እንዴት ባሉ ክፉ ቃላት በእኛ ላይ እንደተናገረ አልረሳም።ይህም አልበቃ ብሎት ወንድሞችን አይቀበልም ሊቀበሉ የሚፈልጉትንም ይከለክላቸዋል ከቤተክርስቲያንም ያስወጣቸዋል።
\s5
\v 11 የተወደድክ ሆይ መልካሙን እንጂ ክፉን አትምሰል። መልካም የሚያደርግ ሁሉ ከእግዚአብሔር ነው። ክፉን የሚያደርግ ሁሉ እግዚአብሔርን አላየውም።
\v 12 ለዲሜጥሮስ ሁሉም ይመሰክሩለታል እውነት እራሷም ትመሰክርለታልች። እኛም እንመሰክርለታለን የኛ ምስክርነት ደግሞ እውነት እንደሆነ ታውቃላችሁ።
\s5
\v 13 የምጽፍልህ ብዙ ነገር ነበረኝ ነገር ግን በወረቀትና በቀለም ልጽፍልህ አልፈለግሁም።
\v 14 ይልቁኑ ልጎበኝህ አስባለሁና በዚያን ጊዜ ፊት ለፊት እንነጋገራለን።
\v 15 ሠላም ለአንተ ይሁን። ወገኖችሰላምታ ያቀርቡልሀል። በአንተ ዘንድ ላሉት ወገኖች በስማቸው እየጠራህ ሠላምታ አቅርብልኝ።