am_ulb/42-MRK.usfm

1271 lines
112 KiB
Plaintext

\id MRK
\ide UTF-8
\h ማርቆስ
\toc1 ማርቆስ
\toc2 ማርቆስ
\toc3 mrk
\mt ማርቆስ
\s5
\c 1
\cl ምዕራፍ 1
\p
\v 1 ልጅ የኢየሱስ ክርስቶስ ወንጌል መጀመሪያ፡፡
\v 2 በነብዩ በኢሳይያስ እንደተጻፈው እነሆ! መንገድን የሚያዘጋጅላችሁን መልዕክተኛዬን በፊታችሁ እልካለሁ፤
\v 3 መንገድን አዘጋጁ ጥርጊያውንም አቅኑ ብሎ በምድረበዳ የሚጮህ ሰው ድምፅ፡፡
\s5
\v 4 በምድረበዳ እያጠመቀና ለኃጢአት ይቅርታ የንሰሐን ጥምቀት እየሰበከ መጣ፡፡
\v 5 ሁሉና በኢየሩሳሌም ያሉ ሁሉ ወደ እርሱ ወደ ዮርዳኖስ ወንዝ እየመጡ ኃጢአታቸውን በመናዘዝ ይጠመቁ ነበር፡፡
\v 6 የግመል ጠጉር ይለብስና ወገቡን በቆዳ መታጠቂያ ይታጠቅ፣ አንበጣና የበረሃ ማርም ይበላ ነበር፡፡
\s5
\v 7 የጫማውን ማሰሪያ ለመፍታት የማልበቃ ከእኔ ይልቅ ታላቅ የሆነ እርሱ ከበስተኋላዬ ይመጣል፡፡
\v 8 በውሃ አጥምቄአችኋለሁ፤ እርሱ ግን በመንፈስ ቅዱስ ያጠምቃችኋል እያለ ይሰብክ ነበር፡፡
\s5
\v 9 ቀናት ኢየሱስ ከገሊላ ናዝሬት በመምጣት በዮርዳኖስ ውስጥ በዮሐንስ ተጠመቀ፡፡
\v 10 እንደወጣም ሰማይ ሲከፈት፣ መንፈስ ቅዱስም እንደ እርግብ በእርሱ ላይ ሲወርድ አየ፤
\v 11 ልጄ አንተ ነህ፤ በአንተ ደስ ይለኛል የሚል ድምጽም ከሰማያት መጣ፡፡
\s5
\v 12 መንፈስ ቅዱስ ወደ ምድረበዳ መራው፡፡
\v 13 በሰይጣን እየተፈተነም በምድረበዳ ለአርባ ቀን ቆየ፡፡ ከዱር አራዊትም ጋር ነበረ፤ መላዕክትም አገለገሉት፡፡
\s5
\v 14 ታልፎ ከተሰጠ በኋላ ኢየሱስ የእግዚአብሔርን የምሥራች ቃል እየሰበከ ወደ ገሊላ መጣ፡፡
\v 15 ተፈጸመ፤የእግዚአብሔር መንግሥት ቀርባለችና ንሰሐ ግቡ፤ በወንጌልም እመኑ ይል ነበር፡፡
\s5
\v 16 ባህር ዳር ሲያልፍ ሳለ ስምዖን ጴጥሮስንና ወንድሙን እንድርያስን መረባቸውን ወደ ባህር ሲጥሉ አያቸው፤ አሳ አጥማጆች ነበሩና፡፡
\v 17 በኋላዬ ኑና ሰዎችን የምታጠምዱ አደርጋችኋለሁ አላቸው፡፡
\v 18 መረቦቻቸውን ትተው ተከተሉት፡፡
\s5
\v 19 እልፍ እንዳለም የዘብዴዎስን ልጅ ያዕቆብንና ወንድሙን ዮሐንስን እነርሱም በጀልባቸው ውስጥ መረቦቻቸውን ሲጠግኑ አያቸው፡፡
\v 20 ጠራቸው፤ እነርሱም ዘብዴዎስ አባታቸውን ከተቀጣሪ ሰራተኞቻቸው ጋር በጀልባው ውስጥ ትተው ተከተሉት፡፡
\s5
\v 21 ቅፍርናሆም ሔዱ፡፡ ወዲያው በሰንበት ቀን ወደ ምኩራብ ገብቶ አስተማራቸው፡፡
\v 22 ጸሐፍት ሳይሆን ትምህርቱ እንደ ባለሥልጣን ስለነበረ በትምህርቱ ተገረሙ፡፡
\s5
\v 23 ርኩስ መንፈስ ያለበት አንድ ሰው በምኩራባቸው ነበረ፡፡
\v 24 የናዝሬቱ ኢየሱስ ሆይ! ከአንተ ጋር ምን አለን? ልታጠፋን መጣህን? ማን እንደሆንክ አውቄሃለሁ፤ አንተ የእግዚአብሔር ቅዱስ ብሎ ጮኸ፡፡
\v 25 ዝም በል! ከእርሱም ውጣ ብሎ ገሰጸው፡፡
\v 26 መንፈስ መሬት ላይ ጥሎ ካንፈራገጠው በኋላ በታላቅ ድምጽ ጮኾ ወጣ፡፡
\s5
\v 27 ሁሉ በጣም ተገረሙና ይህ አዲስ ትምህርት ምንድነው? ርኩሳን መናፍስትን እንኳን በሥልጣን ያዛቸዋልና እነርሱም ይታዘዙለታል በማለት እርስ በርሳቸው ተጠያየቁ፡፡
\v 28 እርሱም በገሊላ አውራጃና በዙሪያው ባሉ ሀገራት ሁሉ ዝናው ወጣ፡፡
\s5
\v 29 እንደወጡ ወዲያው ከዮሐንስና ከያዕቆብ ጋር ወደ ስምዖንና እንድርያስ ቤት መጡ፡፡
\v 30 ጊዜ የስምዖን አማት አተኵሷት ተኝታ ነበርና ወዲያው ስለ እርስዋ ነገሩት፡፡
\v 31 እጇን ይዞ አስነሳት፤ ወዲያውኑ ትኵሳቱ ለቀቃትና አገለገለቻቸው፡፡
\s5
\v 32 ጠልቃ በመሸ ጊዜም ብዙ በሽተኞችንና በአጋንንት የተያዙትን ወደ እርሱ አመጧቸው፡፡
\v 33 ሰው ሁሉ በአንድነት በቤቱ ደጃፍ ተከማችቶ ነበር፡፡
\v 34 በተለያየ በሽታ የታመሙትን ፈወሳቸው፤ ብዙ አጋንንንትንም አወጣ፡፡ አጋንንቱ ማን መሆኑን አውቀውት ነበርና እንዳይገልጡት አዘዛቸው፡፡
\s5
\v 35 እጅግ በማለዳ ተነስቶ ለብቻው ወደ ምድረበዳ ሔደና ጸለየ፡፡
\v 36 ከእርሱ ጋር የነበሩትም ተከተሉት፡፡
\v 37 ጊዜ ሕዝቡ ሁሉ ይፈልጉሃል አሉት፡፡
\s5
\v 38 የምሥራቹን ቃል እንድሰብክ ወደ ሌሎቹ ከተሞች ደግሞ እንሂድ፣ ስለዚህ ጉዳይ መጥቻለሁና አላቸው፡፡
\v 39 ወዳሉ ምኩራቦቻቸው ሁሉ እየገባ ሰበከላቸው፣ አጋንንትንም አወጣ፡፡
\s5
\v 40 ለምጻም ወደ እርሱ መጥቶ ሰገደለትና ብትፈቅድስ ልታነጻኝ ትችላለህ ብሎ ለመነው፡፡
\v 41 አዘነለት፤ እጁን ዘርግቶ ዳሰሰውና እፈቅዳለሁ፣ ንጻ! አለው፡፡
\v 42 ለምጹ ለቀቀውና ንጹህ ሆነ፡፡
\s5
\v 43 ለማንም እንዳይናገር አጥብቆ አዘዘውና ወዲያው ሲያሰናብተው ሳለ
\v 44 ግን ራስህን ለካህን አሳይ፤ ስለመንጻትህ ምሥክር እንዲሆንባቸው ሙሴ ያዘዘውን መስዋዕት አቅርብ አለው፡፡
\s5
\v 45 ግን ሄደና ኢየሱስ በግልጽ ወደ ከተማ ለመግባት እስኪሳነው ድረስ ስለዚህ ነገር አብዝቶ ሊያወራና ሊያሰራጭ ጀመረ፡፡ በመሆኑም በምድረበዳ አካባቢዎች እንዲቆይ ሆነ፤ ሰዎችም ከየአቅጣጫው ወደ እርሱ ይመጡ ነበር፡፡
\s5
\c 2
\cl ምዕራፍ 2
\p
\v 1 ቀናት በኋላ ኢየሱስ ወደ ቅፍርናሆም ተመልሶ በመጣ ጊዜ፣ በቤት እንዳለ ወሬው ተሰማ፡፡
\v 2 ሰዎችም ተሰበሰቡ፤ከዚህ የተነሣ በበሩ መግቢያም እንኳ በቂ ቦታ አልነበራቸውም፡፡ ኢየሱስም የእግዚአብሔርን ቃል ነገራቸው፡፡
\s5
\v 3 ሰዎችም አንድ ሽባ ሰው ወደ እርሱ አመጡ፡፡
\v 4 ብዛት ምክንያት ወደ እርሱ መቅረብ ስላልቻሉ፣ኢየሱስ ባለበት አቅጣጫ ጣሪያውን ነደሉት፡፡ በቀዳዳውም ሽባው ያለበትን ዐልጋ ወደ ታች አወረዱት፡፡
\s5
\v 5 እምነታቸውን አይቶ ሽባውን ሰው፣ "አንተ ልጅ ኀጢአትህ ተሰርዮልሃል" አለው፡፡
\v 6 ግን አንዳንድ ጸሓፍት በዚያ ተቀምጠው ነበር፡፡ ይህ ሰው እንዲህ ብሎ የሚናገረው ለምንድን ነው? እርሱ እግዚአብሔርን ይሳደባል፤
\v 7 ከእግዚአብሔር በቀር ኀጢአትን ይቅር ማለት የሚችል ማን ነው? እያሉ በልባቸው ያጉረመርሙ ነበር፡፡
\s5
\v 8 ኢየሱስ በውስጣቸው እያጉረመረሙ እንደሆነ በመንፈሱ ዐውቆ፣ "በልባችሁ የምታጉረመርሙት ለምንድን ነው? አላቸው፡፡
\v 9 ለሽባው ሰው የትኛውን ማለት ይቀላል? ኀጢኣትህ ተሰርዮልሃል ወይስ ተነሣ ዐልጋህን ተሸክመህ ሂድ ማለት?
\s5
\v 10 እንጂ የሰው ልጅ በምድር ላይ ኀጢኣትን የማስተሰረይ ሥልጣን እንዳለው እንድታውቁ፣
\v 11 እልሃለሁ፤ ተነሣ! ዐልጋህን ተሸከምና ወደ ቤትህ ሂድ" አለው፡፡
\v 12 እርሱም ተነሣ፤ ወዲያውኑም ዐልጋውን ተሸክሞ በሁሉም ፊት ወጥቶ ሄደ፡፡በዚያ የነበሩትም ሁሉም ተገርመው ስለ ነበር እንዲህ ያለ ነገር ፈጽሞ አይተን አናውቅም በማለት እግዚአብሔርን አከበሩ፡፡
\s5
\v 13 ወደ ባሕሩ ዳርቻ ሄደ፡፡ሕዝቡም በሙሉ ወደ እርሱ ተሰበሰቡ፤ አስተማራቸውም፡፡
\v 14 ሲያልፍም የእልፍዮስን ልጅ ሌዊን ቀረጥ በመሰብሰቢያ ቦታው ተቀምጦ አየውና "ተከተለኝ" አለው፡፡ ተነሥቶም ተከተለው፡፡
\s5
\v 15 በእርሱ(በሌዊ) ቤት ተቀምጦ እየበላ ነበር፡፡ ብዙ ቀራጮችና ኀጢአተኞችም ከኢየሱስና ከደቀመዛሙርቱ ጋር ተቀመጡ፤ ብዙዎቹም ተከትለውት ነበርና፡፡
\v 16 ጸሓፍትም ከኀጢአተኞችና ከቀራጮች ጋር ሲበላ ሲያዩት ደቀመዛሙርቱን፣ "እርሱ ከቀራጮችና ከኀጢአተኞች ጋር የሚበላውና የሚጠጣው እንዴት ነው" አሏቸው፡፡
\s5
\v 17 ይህን ሲሰማ፣ "ሕሙማን እንጅ ጤናሞች ሐኪም አያስፈልጋቸውም" ፤ እኔ ኀጢአተኞችን እንጂ ጻድቃንን ልጠራ አልመጣሁም አላቸው፡፡
\s5
\v 18 ደቀመዛሙርትና ፈሪሳውያን ይጾሙ ነበር፡፡ ወደ እርሱም መጥተው የዮሐንስ ደቀመዛሙርትና የፈሪሳውያን ደቀመዛሙርት የሚጾሙት ነገር ግን የአንተ ደቀመዛሙርት የማይጾሙት ለምንድን ነው? አሉት፡፡
\v 19 እንዲህ አላቸው፡፡ሙሽራው አብሮአቸው ሳለ ሚዜዎቹ ይጾማሉ? ሙሽራው ከእነርሱ ጋር እስካለ ሊጾሙ አይችሉም፡፡
\s5
\v 20 ግን ሙሽራው የሚወሰድበት ቀን ይመጣል፡፡ በዚያን ጊዜ በዚያ ቀን ይጾማሉ፡፡
\v 21 አዲስ እራፊ ጨርቅ በዐሮጌ ልብስ ላይ አየይጥፍም፤ ያለበለዚያ የተጣፈው እራፊ ይቀደዳል፡፡ ቀዳዳውም የባሰ ይሆናል፡፡
\s5
\v 22 የወይን ጠጅ በዐሮጌ ዐቁማዳ ውስጥ የሚያስቀምጥ ማንም ለም፡፡ አለበለዚያ የወይን ጠጁ ዐቁማዳውን ያፈነዳዋል፤የወይን ጠጁና ዐቁማዳውም ይበላሻሉ፡፡ ነገር ግን አዲስ የወይን ጠጅ በአዲስ ዐቁማዳ ውስጥ ያስቀምጣሉ፡፡
\s5
\v 23 በሰንበት ቀን በእህል ማሳ መካከል ያልፍ ነበር፡፡ ደቀመዛሙርቱም ሲያልፉ እሸት መቅጠፍ ጀመሩ፡፡
\v 24 ፈሪሳውያንም እነሆ በሕግ ያልተፈቀደውን በሰንበት የሚያደርጉት ለምንድን ነው? አሉት፡፡
\s5
\v 25 እንዲህ አላቸው፡፡ ዳዊት በተራበና በተቸገረ ጊዜ ለራሱና አብረውት ለነበሩት ምን እንዳደረገ፣ አብያታር ሊቀ ካህናት በነበረ ጊዜ ወደ እግዚአብሔር ቤት እንደገባ፤
\v 26 ብቻ የተፈቀደውን ገጸ ኅብስት እንደ በላ፣ ከእርሱም ጋር ለነበሩት እንደሰጣቸው ፈጽሞ አላነበባችሁምን? እንዲህም አላቸው፡፡
\s5
\v 27 የተፈጠረው ለሰው ነው እንጂ ሰው ለሰንበት አልተፈጠረም፡፡
\v 28 የሰው ልጅ የሰንበትም እንኳ ጌታ ነው፡፡
\s5
\c 3
\cl ምዕራፍ 3
\p
\v 1 ምኩራብም ደግሞ ገባ፤ በዚያም እጁ የሰለለችበት ሰው ነበረ፡፡
\v 2 ሰውየውን በሰንበት ቀን ይፈውሰው እንደሆነ ተመለከቱት፡፡
\s5
\v 3 የሰለለችበትን ሰውየም ተነሥ አለው፡፡
\v 4 ሕዝቡንም በሰንበት ቀን የተፈቀደው መልካም ማድረግ ነው ወይስ ክፉ ማድረግ? ሕይወትን ማዳን ወይስ ማጥፋት? አላቸው፡፡ ነገር ግን ሕዝቡ ዝም አሉ፡፡
\s5
\v 5 በቁጣ ሲመለከት፣ በልባቸው ድንዳኔ ዐዝኖ፣ ሰውየውን እጅህን ዘርጋ አለው፤ ዘረጋውም፤ ዳነም፡፡
\v 6 ወጡ፤ ወዲውም እንዴት ሊያጠፉት እንደሚችሉ ከሄሮድስ ወገኖች ጋር በእርሱ ላይ ተማከሩ፡፡
\s5
\v 7 ከደቀ ዛሙርቱ ጋር ወደ ባሕሩ ሄደ፤ ከገሊላም እጅግ ብዙ ሕዝብ ተከትለው፤ ከይሁዳና
\v 8 ከኤዶምያስና ከዮርዳኖስ ማዶ፣ ከጢሮስና ከሲዶና ምን ታላላቅ ነገሮችን እንዳደረገ በመስማት እጅግ ብዙ ሕዝብ ወደ እርሱ መጣ፡፡
\s5
\v 9 የተነሣ እንዳያጨናንቁት ትንሽ ጀልባ እንዲያቆዩለት ለደቀ መዛሙርቱ ተናገረ፤
\v 10 ፈውሶ ነበርና፡፡ በብዙ ደዌ የሚሠቃዩ ሁሉ ሊዳስሱት ይጋፉት ነበር፡፡
\s5
\v 11 መናፍስትም ባዩት ጊዜ በፊቱ ወደቁ፤ አንተ የእግዚአብሔር ልጅ ነህ እያሉም ጮኹ፡፡
\v 12 ግን ማንነቱን እንዳይገልጡት አጥብቆ አዘዛቸው፡፡
\s5
\v 13 ወደ ተራራውም ወጣ፤ የሚፈልጋቸውንም ወደ እርሱ ጠራ፤ እነርሱም ወደ እርሱ ሄዱ፡፡
\v 14 ጋር እንዲሆኑ፣ ለመስበክ እንዲልካቸውና
\v 15 ለማስወጣት ሥልጣን እንዲኖራቸው
\v 16 ሁለት ሾመ፤ ጴጥሮስ ብሎ የሰየመው ስምዖን፣
\s5
\v 17 ልጅ ያዕቆብና የያዕቆብ ወንድም ዮሐንስ፤ እነርሱንም ቦአኔርጌስ ብሎ ጠራቸው፤ የነጎድጓድ ልጆች ማለት ነው፤
\v 18 እንድርያስና ፊልጶስ፣ በርተሎሜዎስና ማቴያስ፣ ቶማስና የእልፍዮስ ልጅ ያዕቆብ፣ ታዴዎስ፣ ቀናተኛው ስምኦንና
\v 19 የሰጠው የአስቆሮቱ ይሁዳ፡፡
\s5
\v 20 ኢየሱስ ወደ አንድ ቤት ውስጥ ገባ፡፡ መብላት እንኳ እስከማይችሉ ድረስ እንደ ገና ብዙ ሕዝብ መጥቶ ተሰበሰበ፡፡
\v 21 ዘመዶቹም በሰሙ ጊዜ ይዘውት ሊሄዱ ወደ እርሱ መጡ፤ ዐብዶአል ብለው ነበርና፡፡
\v 22 የወረዱ ጻፎችም ብዔልዜቡል አለበት፤ አጋንንንትን የሚያስወጣውም በአጋንንት አለቃ ነው አሉ፡፡
\s5
\v 23 እርሱ ጠርቶአቸውም በምሳሌ ነገራቸው፤ ሰይጣን እንዴት ሰይጣንንን ማስወጣት ይችላል?
\v 24 መንግሥትም እርስ በርሱ ቢከፋፈል፣ ያ መንግሥት መቆም አይችልም፤
\v 25 ቤትም እርስ በርሱ ቢለያይ፣ ያ ቤት ጸንቶ ሊቆም አይችልም፡፡
\s5
\v 26 ሰይጣንም እርስ በርሱ ቢቀዋወምና ቢለያይ፣ ፍጻሜው ይሆናል እንጂ መቆም አይችልም፡፡ በመጀመሪያ ኀይለኛውን ሰው ካላሰረና ከዚያም ንብረቱን ካልዘረፈ በቀር፣
\v 27 ወደ ኀይለኛው ቤት መግባትና ንብረቱን መዝረፍ የሚችል የለም፡፡
\s5
\v 28 እላችኋለሁ፤ ለሰው ልጆች ኀጢአታቸው ሁሉ፣ የሚሳደቡትም ስድብ ሁሉ ይቅር ይባላል፤
\v 29 ቅዱስን የሚሳደብ ግን ፈጽሞ ይቅርታ አያገኝም፤ ይልቁንም የየዘለዓለም ኀጢአት ዕዳ አለበት፤
\v 30 ርኩስ መንፈስ አለበት ብለዋል፡፡
\s5
\v 31 ወንድሞቹም መጡ፤ ውጭ ቆመውም እንዲጠሩት ወደ እርሱ ላኩ፡፡
\v 32 ብዙ ሰው ተቀምጦ ነበር፤ ሰዎችም እነሆ፣ እናትህና ወንድሞችህ ውጭ ይፈልጉሃል አሉት፡፡
\s5
\v 33 መለሰላቸው፤ አላቸውም፣ እናቴና ወንድሞቼ ማን ናቸው?
\v 34 ዙሪያ የተቀመጡትን ተመልክቶም፣ እነሆ እናቴና ወንድሞቼ! ምክንያቱም
\v 35 ፈቃድ የሚፈጽም ሁሉ ወንድሜ፣ እኅቴና እናቴ ነው፡፡
\s5
\c 4
\cl ምዕራፍ 4
\p
\v 1 በባህር አጠገብ ማስተማር ጀመረ፡፡ ከህዝቡ መብዛት የተነሳ በባህር ላይ ባለ ጀልባ ገብቶ ተቀመጠ፡፡ ህዝቡም ሁሉ በባህሩ ዳርቻ ላይ ተሰብስበው ነበር፡፡
\v 2 ነገርም በምሳሌ አስተማራቸው፡፡ በትምህርቱም እንዲህ አላቸው፡፡
\s5
\v 3 ስሙ ዘሪ ሊዘራ ወጣ፡፤
\v 4 በሚዘራበትም ጊዜ አንዳንዱ በመንገድ ዳር ወደቀ ወፎችም መጥተው ለቀሙት፡፡
\v 5 ደግሞ ብዙ አፈር በሌለው በድንጋያማ መሬት ላይ ወደቀ፡፡ መሬቱ ጥልቀት ስላልነበረው ወዲያው በቀለ፤
\s5
\v 6 በወጣ ጊዜም ጠወለገ ሥርም ስላልነበረው ደረቀ፡፡
\v 7 ደግሞም አንዳንዱ በእሾህ መካከል ወደቀ እሾሁም አድጎ አነቀው ፍሬም አላፈራም፡፡
\s5
\v 8 አንዳንዱ በመልካም መሬት ላይ ወደቀ አደገ እየበዛ ሄደ ፍሬም አፈራ ሶስት እጥፍ ስልሳ እጥፍ እና መቶ እጥፍ ፍሬ ሰጠ፡፡
\v 9 እንዲህም አለ ጆሮ ያለው ይስማ፡፡
\s5
\v 10 በሆነ ጊዜ ከደቀመዛሙርቱ ጋር አብረው የነበሩት ስለ ምሳሌዎቹ ጠየቁት፡፡
\v 11 አላቸው ለእናንተ የእግዚአብሔር መንግሥት ምስጢር ተሰጥቷችኋል፡፡ በውጭ ላሉት ግን እንዲህ አይደለም
\v 12 እንዳያዩ ሰምተውም እንዳያስተውሉ እንደገና ተመልሰው ይቅር እንዳይባሉ ሁሉም ነገር በምሳሌ ይሆንባቸዋል፡፡
\s5
\v 13 አላቸው እናንተ ይህ ምሳሌ አልገባችሁምን? ሌሎቹን ምሳሌዎች ሁሉ እንዴት ትረዳላችሁ?
\v 14 ዘሪው ቃሉን ዘራ፡፡
\v 15 በመንገድ ዳር የወደቁት እነዚህ ናቸው ቃሉ በሚዘራበት ጊዜና ቃሉን እንደሰሙ ወዲያውኑ ሰይጣን መጥቶ በውስጣቸው የተዘራውን ቃል ይወስዳል፡፡
\s5
\v 16 በድንጋያማ መሬት ላይ የወደቁት አነዚህ ቃሉን በሰሙ ጊዜ ወዲያውኑ በደስታ ይቀበሉታል
\v 17 ሥር የላቸውምና ለጊዜው ይቀበሉታል ከዚያም በቃሉ ምክንያት መከራ ወይም ስደት በሚነሳበት ጊዜ ወዲያወኑ በቃሉ ይሰናከሉበታል፡፤
\s5
\v 18 ቦታ የወደቁት እነዚህ ቃሉን የሰሙ ናቸው
\v 19 አለም ሀሳብና የባለጠግነት ማታለል የሌሎች ነገሮች ምኞት ይገቡና ዘሩን ያንቁታል ፍሬ የማያፈራም ይሆናል፡፡
\v 20 መሬት የወደቁት እነዚህ ቃሉን ሰምተው የሚቀበሉት ናቸው ሰላሳ እጥፍ ስልሳ እጥፍ እና መቶ እጥፍ የሚያፈሩ ናቸው፡፡
\s5
\v 21 አላቸው፡- መብራትን ከፍ ባለ ማስመጫ ላይ እንጂ ከእንቅብ በታች ወይም አልጋ ሥር ያስቀምጡታልን?
\v 22 ሳይገለጥ የሚቀር ነገር የለም በሚስጢር የተደረገ ወደ ብርሃንም የማይወጣ የለም፡፡
\v 23 ያለው ይስማ እንዲህም አላቸው
\s5
\v 24-25 አስተውሉ መስፈሪያ ይሰፈርላችኋል ለእናንተም የበለጠ ይሰጣችኋል፡፡ ላለው የበለጠ ይጨመርለታል ከሌለው ግን ያ ያለው እንኳ ይወሰድበታል፡፡
\s5
\v 26 አለ የእግዚአብሔር መንግሥት በመሬት ላይ ዘርን የዘራን ሰው ትመስላለች፡፡
\v 27 ሲመሽ ይተኛል ሲነጋም ይነቃል፡፡ እንዴት እንደሆነ ባላወቀው መልኩ ዘሩ አቆትቁጦ በቀለ፡፤
\v 28 ምድር የራሷን ሰብል ፍሬ አፈራች መጀመሪያ ቅጠሉ ቀጥሎም ዛላው በመጨረሻም በዛላው ውስጥ ሙሉ ፍሬ አፈራች፡፡
\v 29 ግን ፍሬው በደረሰ ጊዜ መከር ነውና ወዲያውኑ ማጭድ አዘጋጀ፡፡
\s5
\v 30 እንዲህ አለ የእግዚአብሔርን መንግሥት በምን እንመስላታለን? ወይም በምን ምሳሌ እንገልጻታለን?
\v 31 ቅንጣት ትመስላለች፡፡ በምድር ላይ በተዘራ ጊዜ ሲዘራ ምንም እንኳ በምድር ካሉ ዘሮች ሁሉ ያነሰ ቢሆንም
\v 32 ጊዜ ያድጋል ቅርንጫፍም ያወጣል የሰማይ ወፎች ከጥላው ሥር እስኪጠለልቡበት ድረስ ከተክሎች ሁሉ ይልቅ ታላቅ ይሆናል፡፡
\s5
\v 33 ሊሰሙ በሚችሉት መጠን ቃሉን በብዙ ምሳሌዎች ተናገራቸው
\v 34 ምሳሌ ምንም አልተናገራቸውም፡፡ ለደቀመዛሙርቱ ግን ለብቻቸው ሁሉንም ነገር ገለጸላቸው፡፡
\s5
\v 35 ቀን በመሸ ጊዜ ወደ ማዶ እንሻገር አላቸው፡፡
\v 36 ህዝቡንም ትተው በጀልባ ወሰዱት፡፡ ሌሎችም ጀልባዎች ከእርሱ ጋር ነበሩ፡፡
\v 37 የነፋስ ማዕበልም ተነሳ ጀልባው እስኪጥለቀለቅ ድረስ ማዕበል ጀልባውን መታው፡፡
\s5
\v 38 ከጀልባው በስተኋለኛው ክፍል ትራስ ተንተርሶ ተኝቶ ነበር፡፡ ቀስቅሰውም መምህር ሆይ ስንጠፋ አይገድህምን አሉት፡፡
\v 39 እርሱም ተነሳ ነፋሱንም ገሰጸው ባህሩንም ዝም በል ጸጥ በል አለው፡፡ ነፋሱም ተወ ታላቅ ጸጥታም ሆነ፡፡
\s5
\v 40 ስለምን ፈራችሁ? እምነት የላችሁምን እምነታችሁስ ወዴት አለ አላቸው፡፡
\v 41 ፈርተው እርስ በእርሳቸው ነፋሱና ባህሩ እንኳ የሚታዘዙለት እንግዲህ ይህ ማነው? ተባባሉ፡፡
\s5
\c 5
\cl ምዕራፍ 5
\p
\v 1 ባሕሩ ሌላ ዳርቻ፣ ወደ ጌርጌሴኖን አገር መጡ፡፡
\v 2 ከጀልባዋ ውስጥ ሲወጣም ወዲያውኑ ርኩስ መንፈስ ያለበት አንድ ሰው ከመቃብር ሥፍራ ወጥቶ ተገናኘው፤
\s5
\v 3 በመቃብር ስፍራ አድርጎ ነበር፤ እርሱን በሰንሰለት ሊያስረው የሚችል ሰው አልነበረም፤
\v 4 ጊዜ በእግር ብረትና በሰንሰለት ይታሰር ስለ ነበር፣ ሰንሰለቶቹን ይበጣጥሳቸው፣ እግር ብረቶቹንም ይሰባብራቸው ነበር፤ እርሱን ለመያዝ የሚያስችል ጥንካሬ ያለው ሰውም አልነበረም፡፡
\s5
\v 5 ቀንና ሌሊት በመቃብሮቹና በተራራዎቹ ዘንድ ሰውነቱን በድንጋይ እየቈረጠ ይጮኽ ነበር፡፡
\v 6 ከሩቅ ሲያየው፣ ሮጠና ሰገደለት፤
\s5
\v 7 በመጮኽም፣ የልዑል እግዚአብሔር ልጅ ኢየሱስ ከአንተ ጋር ምን አለኝ? በእግዚአብሔር አምልሃለሁ፣ አታሠቃየኝ አለ፡፡
\v 8 ርኩስ መንፈስ ከሰውየው ውጣ ብሎት ነበርና፡፡
\s5
\v 9 ማን ነው ብሎም ጠየቀው፤ ብዙ ነንና ስሜ ሌጌዎን ነው አለው፡፡
\v 10 እንዳያባርራቸውም አጥብቆ ለመነው፡፡
\s5
\v 11 በተራራው ጥግ ትልቅ የእሪያ መንጋ ይሰማራ ነበር፡፡
\v 12 በእነርሱ ውስጥ እንድንገባ ወደ እሪያዎቹ ስደደን በማለትም ለመኑት፡፡
\v 13 እዲሄዱ ፈቀደላቸው፡፡ ርኩሳን መናፍስቱም ወጡ፣ በእሪያዎቹም ውስጥ ገቡ፤ ሁለት ሺ ያህል እሪያ ያለበት መንጋም በቁልቁለቱ ላይ ወደ ባሕሩ እየተንጋጋ ሄደ፤ በባሕሩም ውስጥ ሰመጠ፡፡
\s5
\v 14 የሚጠብቁትም ሸሹ፤ በከተማውና በአገሩ ውስጥም አወሩት፡፡ የሆነውንም እንዴት እንደ ነበረ ለማየትም ሰዎች መጡ፡፡
\v 15 ኢየሱስም መጥተው አጋንንት ያደሩበትን፣ ሌጌዎንም እንኳ የነበረበትን ሰው ተቀምጦ፣ ልብስ ለብሶና ልቡም ተመልሶለት አይተው ፈሩ፡፡
\s5
\v 16 ሰዎችም አጋንንት ባደሩበት ሰውየ ላይ የታየው እንዴት እንደ ሆነና በእሪያዎቹ የሆነውም እንዴት እንደ ነበረ ነገሯቸው፡፡
\v 17 ኢየሱስንም ከአገራቸው እንዲወጣ ይለምኑት ጀመር፡፡
\s5
\v 18 ጀልባዋ ውስጥ እየገባ ሳለ፣ በአጋንንት ተይዞ የነበረው ሰው ከአንተ ጋር ልኑር ብሎ ለመነው፡፡
\v 19 አልፈቀደለትም፤ ይልቁንም ወደ ቤትህ፣ ወደ ዘመዶችህ ሂድ፣ ጌታ ለአንተ እንዴት ታላላቅ ነገሮችን እንዳደረገልህ፣ እንዴትም ምሕረቱን ባንተ ላይ እንዳሳየ ንገራቸው አለው፡፡
\v 20 ሄደና ኢየሱስ እንዴት ታላላቅ ነገሮችን እንዳደረገለት ዐሥር ከተማ በሚባለው ውስጥ ማሠራጨት ጀመረ፤ ሰዎችም ሁሉ ተደነቁ፡፡
\s5
\v 21 በጀልባዋ ወደ ሌላ አቅጣጫ ይሄድ በነበረ ጊዜም ደግሞ፣ እጅግ ብዙ ሕዝብ ወደ እርሱ ተሰበሰበ፤ እርሱም በባሕሩ አቅራቢያ ነበረ፡፡
\v 22 ከምኵራብ ኀላፊዎች አንዱ፣ ኢያኢሮስ የሚባል መጣ፣ እርሱንም አይቶ በእግሩ ሥር ወደቀ፤
\v 23 ልጄ ልትሞት ነው፤ እንድትድንና በሕይወት እንድትኖር መጥተህ እጅህን ትጭንባት ዘንድ እለምንሃለሁ በማለትም አጥብቆ ለመነው፡፡
\v 24 ዐብሮት ሄደ፤ እጅግ ብዙ ሰዎችም ተከተሉት፤ ይጋፉትም ነበር፡፡
\s5
\v 25 ሁለት ዓመት ደም ይፈስባት የነበረ፣
\v 26 ብዙ ችግር የደረሰባት ብትሆንና ያላትን ሁሉ ብትከፍልም፣ ምንም ያልተሻላት፣ ይልቁንም የባሰባት
\v 27 ሴት ስለ ኢየሱስ ሰምታ ከሕዝቡ በስተኋላ መጣች፣ የኢየሱስንም ልብስ ነካች፡፡
\s5
\v 28 ላት፣ ይልቁንም የባሰባት 27አንድ ሴት ስለ ኢየሱስ ሰምታ ከሕዝቡ በስተኋላ መጣች፣ የኢየሱስንም ልብስ ነካች፡፡ 28ልብሱን ብቻ ከነካሁ እድናለሁ ብላለችና፡፡
\v 29 የሚፈስሰው ደሟ ቆመ፤ ከሕማሟ እንደ ተፈወሰችም በሰውነቷ ታወቃት፡፡
\s5
\v 30 ኢየሱስ ኀይል ከእርሱ መውጣቱን በራሱ በመረዳት፣ ዙሪያውን ወደ ሕዝቡ ተመለከተ፤ ልብሴን የነካው ማን ነው? ብሎም ተናገረ፡፡
\v 31 መዛሙርቱም ሕዝቡ ሲጋፉህ ታያለህ፣ የነካኝ ማን ነውም? ትላለህ፡፡
\v 32 ይህን ያደረገችውንም ለማየት ዙሪያውን ተመለከተ፡፡
\s5
\v 33 ሴትዮዋ ግን በመፍራትና በመንቀጥቀጥ፣ ለእርሷ የተደረገውንም በማወቅ መጣችና በፊቱ ወደቀች፤ እውነቱንም ሁሉ ነገረችው፡፡
\v 34 እርሱም፡- ልጄ ሆይ! እምነትሽ አድኖሻል፤ በሰላም ሂጂ፣ ከሕማምሽም ተፈወሺ አላት፡፡
\s5
\v 35 ኢየሱስ ገና እየተናገረ ሳለ ከምኵራቡ ኀላፊ ቤት ሰዎች መጡ፤ ልጅህ ሞታለች፤ መምህሩን ለምን ታስቸግረዋለህ ብለውም ተናገሩ፡፡
\s5
\v 36 ኢየሱስ የተናገሩትን ሰምቶ የምኵራቡን ኀላፊ “አትፍራ፤ እመን ብቻ” አለው፡፡
\v 37 ኢየሱስ ከጴጥሮስ፣ ከያዕቆብና ከያዕቆብ ወንድም ከዮሐንስ በቀር ማንም እንዲከተለው አልፈቀደም፡፡
\v 38 ወደ ምኵራቡ ኀላፊ ቤት መጡ፤ ኢየሱስ ያዘኑ፣ የሚያለቅሱና የዋይታ ጩኸት የሚያሰሙ ሰዎችን ተመለከተ፡፡
\s5
\v 39 ወደ ውስጥ ገባና “ለምን ታዝናላችሁ? ለምንስ ታለቅሳላችሁ? ልጅቱ ተኝታለች እንጂ አልሞተችም” አላቸው፡፡
\v 40 ሰዎቹ በኢየሱስ ሣቁበት፤ እርሱ ግን ሁሉንም ወደ ውጭ አስወጣቸው፡፡ የልጅቱን አባትና እናት፣ ከእርሱም ጋር የነበሩትን ይዞ ልጅቱ ወደ ነበረችበት ክፍል ገባ፡፡
\s5
\v 41 ከዚያም ልጅቱን በእጁ ይዞ “ታሊታ ኩም!” ትርጉሙ “ትንሿ ልጅ ተነሺ እልሻለሁ” ማለት ነው፡፡
\v 42 ወዲያው ልጅቱ ተነሣች፤ መራመድም ጀመረች፡፡ (ዐሥራ ሁለት ዓመቷ ነበርና) በዚህ ሰዎቹ በጣም ተገረሙ፡፡
\v 43 ከዚያም ኢየሱስ ስለዚህ ጕዳይ ማንም ማወቅ እንደሌለበት ለሰዎቹ ጥብቅ ትእዛዛትን ሰጣቸው፤ የምትበላውንም ስጧት አለ፡፡
\s5
\c 6
\cl ምዕራፍ 6
\p
\v 1 ከዚያ ወጥቶ ወደ ገዛ ምድሩ መጣ፤ ደቀመዛሙርቱም ተከተሉት፡፡
\v 2 ሰንበት በሆነ ጊዜም በምኩራብ ውስጥ ሊያስተምር ጀመረ፡፡ የሰሙትም ሁሉ ይህ ሰው እነኚህን ነገሮች ከወዴት አገኛቸው? ለዚህ ሰው የተሰጠችውስ ጥበብ እንደምን ያለች ናት፤ በእጆቹ የሚደረጉት እነዚህ ታላላቅ ነገሮችስ ምን ትርጉም ይኖራቸው ይሆን?
\v 3 ይህ አናጺው የማርያም ልጅ፤ የያዕቆብና የዮሳ፣ የይሁዳና የስምዖን ወንድም አይደለምን? እህቶቹስ ቢሆኑ እዚህ ከእኛ ጋር አይደሉምን? በማለት ተደነቁ፤ ተሰናከሉበትም፡፡
\s5
\v 4 ኢየሱስም ነብይ በሀገሩ፣ በወገኑና በገዛ ቤተሰቡ ካልሆነ በስተቀር ሳይከበር አይቀርም አላቸው፡፡
\v 5 ላይ እጆቹን ጭኖ ከመፈወስ በስተቀር በዚያ ታላቅ ተአምራት አላደረገም፡፡
\v 6 ምክንያት ተደነቀ፡፡ በየመንደሮቹም እያስተማረ ዞረ፡፡
\s5
\v 7 አሥራ ሁለቱን ወደ ራሱ ጠራና ሁለት ሁለት አድርጎ ይልካቸው ጀመር፤ በእርኩሳን መናፍስት ላይም ሥልጣንን ሰጣቸው፡፡
\v 8 ለጉዞአቸውም ከበትራቸው በቀር ምግብ፣ የመንገድ ሻንጣም ሆነ በገንዘብ ቦርሳቸው ውስጥ ገንዘብ እንዳይዙ አዘዛቸው፡፡
\v 9 በስተቀር ቅያሪ ልብስ አትያዙ አላቸው፡፡
\s5
\v 10 ከዚያ እስክትወጡ ድረስ በምትገቡበት ቤት በዚያ ቆዩ አላቸው፡፡
\v 11 ቦታ ሁሉ ከማይቀበሏችሁና ከማይሰሟችሁ ሰዎች ምሥክር ይሆንባቸው ዘንድ በጫማችሁ ሥር ያለውን አቧራ አራግፉ፡፡
\s5
\v 12 ደቀ መዛሙርቱም ወጥተው ሰዎች ንሰሐ እንዲገቡ ሰበኩላቸው፡፡
\v 13 ብዙ አጋንንትን አስወጡ፤ ታመው የነበሩ ብዙዎችንም ዘይት ቀብተው ፈወሱአቸው፡፡
\s5
\v 14 ዝናው ወጥቶ ነበርና ንጉሡ ሔሮድስ በሰማ ጊዜ አጥማቂው ዮሐንስ ከሙታን ተነሥቶአል፤ ስለዚህ እነዚህ ታላላቅ ነገሮች የሚደረጉትም በእርሱ ነው አለ፡፡
\v 15 ግን ሌሎች ኤልያስ ነው አሉ፡፡ ሌሎቹም ነብይ ወይም ከነብያት አንዱ ነው አሉ፡፡
\s5
\v 16 ነገር ግን ሔሮድስ ይህንን ሁሉ በሰማ ጊዜ እኔ አንገቱን ያስቆረጥኩት ዮሐንስ ተነሥቶአል አለ፡፡
\v 17 ባገባት በወንድሙ በፊሊጶስ ሚስት በሄሮድያስ ምክንያት ራሱ ልኮ ዮሐንስን በመያዝ በወህኒ አኑሮት ነበርና፡፡
\s5
\v 18 ዮሐንስም ሔሮድስን የወንድምህ ሚስት ለአንተ ልትሆን አይገባም ይለው ነበር፡፡
\v 19 ሔሮድያዳ ዮሐንስን ትቃወምና ልትገድለው ትፈልግ ነበር፣አልቻለችምም፡፡
\v 20 ሔሮድስ ዮሐንስን ይፈራው ነበር፡፡ ቅዱስና ጻድቅ እንደሆነ በማወቁም ይጠነቀቅለት ነበር፡፡ በሚሰማው ጊዜ ግራ እየተጋባም ቢሆን በደስታ ይሰማው ነበር፡፡
\s5
\v 21 ምቹ ቀን በመጣ ጊዜም ልደቱን አስመልክቶ ሔሮድስ ለመኳንንቱ፣ ለሹማምንቱና ለገሊላ ታላላቅ ሰዎች የእራት ግብዣ አዘጋጀላቸው፡፡
\v 22 የሄሮድያዳ ልጅ ራሷ ገብታ በዘፈነች ጊዜም ሔሮድስንና ከእርሱ ጋር በማዕድ የተቀመጡትን አስደሰተቻቸው፡፡ ንጉሱም ልጃገረዲቱን የምትፈልጊውን ሁሉ ጠይቂኝ እሰጥሻለሁ አላት፡፡
\s5
\v 23 ማናቸውንም የምትፈልጊውን ጠይቂኝ፣ የመንግሥቴን ግማሽም ቢሆን እሰጥሻለሁ ብሎ ማለላት፡፡
\v 24 እርስዋም ወጥታ ወደ እናቷ በመሄድ ምን ልጠይቀው? ብትላት የአጥማቂው የዮሐንስን ራስ አለቻት፡፡
\v 25 እርስዋም ወደ ንጉሱ ፈጥና በመምጣት የአጥማቂውን የዮሐንስን ራስ በሳህን እንድትሰጠኝ እፈልጋለሁ አለችው፡፡
\s5
\v 26 ንጉሡም እጅግ አዘነ፡፡ ነገር ግን በመሐላዎቹና በማዕድ በተቀመጡት ምክንያት አልተቃወማትም፡፡
\v 27 ንጉሡም ወዲያውኑ ከጠባቂዎቹ አንደኛውን ወታደር ልኮ ራሱን እንዲያመጣ አዘዘው፡፡ እርሱም ሔደና በወህኒ የዮሐንስን ራስ ቆረጠው፤
\v 28 በሳህን አምጥቶም ለልጃገረዲቱ ሰጣት፣ ልጃገረዲቱም ለእናቷ ሰጠቻት፡፡
\v 29 ደቀመዛሙርቱም ይህንን በሰሙ ጊዜ መጡና አስከሬኑን ወስደው በመቃብር አኖሩት፡፡
\s5
\v 30 ሐዋርያቱም ወደ ኢየሱስ ተመልሰው ያደረጉትንና ያስተማሩትን ነገር ሁሉ ነገሩት፡፡
\v 31 እርሱም እናንተ ራሳችሁ ወደ ምድረበዳ ኑና ጥቂት ጊዜ ዕረፉ አላቸው፡፡ ወደ እነርሱ የሚመጡና የሚሔዱ ብዙዎች ነበሩና ለመብላት እንኳን ጊዜ አጥተው ነበር፡፡
\v 32 በጀልባ ገብተው ወደ ምድረበዳው ፈቀቅ ብለው ሔዱ፡፡
\s5
\v 33 ሲሔዱም ሕዝቡ አዩአቸውና ብዙዎቹ አወቁአቸው፤ እነርሱም ከየከተሞቹ ሁሉ በአንድነት በሩጫ ቀደሟቸው፡፡
\v 34 ወደዚያ በመጣም ጊዜ ብዙ ሕዝብ አይቶ እረኛ እንደሌላቸው በጎች ይመስሉ ነበርና አዘነላቸው፡፡ ብዙ ነገሮችንም ያስተምራቸው ጀመር፡፡
\s5
\v 35 ቀኑ በመሸ ጊዜም ደቀመዛሙርቱ ወደ እርሱ ቀርበው ሥፍራው ምድረበዳ ነው፣ ቀኑም መሽቶአል፤
\v 36 በአቅራቢያው ወደሚገኙ ከተሞችና መንደሮች ሔደው ለራሳቸው አንዳች የሚበሉትን እንዲገዙ ሕዝቡን አሰናብታቸው አሉት፡፡
\s5
\v 37 እርሱ ግን መልሶ እናንተ የሚበሉትን ስጧቸው አላቸው፡፡ እነርሱም እንሂድና ይበሉ ዘንድ የአንድን ሰው የስድስት ወር ገቢ በሚያህል ገንዘብ እንጀራ ገዝተን እንስጣቸውን? አሉት፡፡
\v 38 እርሱም ምን ያህል እንጀራ እንዳላችሁ ሂዱና እዩ አላቸው፡፡ ባወቁ ጊዜም ያለው አምስት እንጀራና ሁለት ዓሳ ነው አሉት፡፡
\s5
\v 39 እርሱም ሁሉን በአረንጓዴው ሣር ላይ በቡድን በቡድን እንዲያስቀምጡ አዘዛቸው፡፡
\v 40 እነርሱም በመቶዎችና በሃምሳዎች እየሆኑ በረድፍ ተቀመጡ፡፡
\v 41 እርሱም አምስቱን እንጀራና ሁለቱን ዓሳ ተቀብሎ ወደ ሰማይ በመመልከት ባረከውና ቆርሶ ለሕዝቡ እንዲያቀርቡት ለደቀመዛሙርቱ ሰጣቸው፡፡ ሁለቱን ዓሳም ለሁሉም አካፈላቸው፡፡
\s5
\v 42 ሁሉም በልተው ጠገቡ፡፡
\v 43 አሥራ ሁለት ትላልቅ መሶብ ሙሉ ቁርስራሽ፣ እንዲሁም ከዓሳው ሰበሰቡ፡፡
\v 44 እንጀራውን የበሉት እነዚያ 5000 ወንዶች ነበሩ፡፡
\s5
\v 45 ወዲያውኑ እርሱ ራሱ ሕዝቡን ሲያሰናብት ሳለ ደቀመዛሙርቱ በጀልባ ገብተው ወደ ማዶ ወደ ቤተሳይዳ ቀድመውት እንዲሻገሩ ግድ አላቸው፡፡
\v 46 ከተለያቸው በኋላም ሊጸልይ ወደ ተራራ ፈቀቅ አለ፡፡
\v 47 በመሸም ጊዜ ጀልባዋ በባህር ላይ ነበረች፤ እርሱም ብቻውን በምድር ላይ ነበር፡፡
\s5
\v 48 ነፋሱ ከፊት ለፊታቸው እየተቃወማቸው ሳለ ለመቅዘፍ ሲጨነቁ አያቸውና ከሌሊቱ በአራተኛው ክፍል በባህሩ ላይ እየተራመደ ወደ እነርሱ መጣ፤ ሊያልፋቸውም ይፈልግ ነበር፡፡
\v 49 ነገር ግን በባህሩ ላይ ሲራመድ ባዩት ጊዜ ምትሃት ነው ብለው ስላሰቡ ጮኹ፡፡
\v 50 ሁሉም አይተውት ስለነበረ ታወኩ፡፡ እርሱ ግን ወዲያው ተናገራቸውና አይዞአችሁ! እኔ ነኝ አትፍሩ! አላቸው፡፡
\s5
\v 51 ወደ እነርሱ ወጥቶም ወደ ጀልባይቱ ገባ፤ ነፋሱም ተወ፡፡
\v 52 እነርሱም በራሳቸው ያለመጠን ተገረሙ፤ ልባቸው ደንዝዞ ነበርና ስለ እንጀራው አላስተዋሉም፡፡
\s5
\v 53 በተሻገሩ ጊዜም ወደ ጌንሳሬጥ አገር ወደ ባህሩ ዳርቻ መጡ፡፡
\v 54 ከጀልባዋ በወጡ ጊዜም ሕዝቡ ወዲያው አወቁትና
\v 55 በዙሪያው ወዳሉ መንደሮች በሞላ በመሮጥ ህሙማንን በአልጋ ተሸክመው እርሱ እንዳለ ወደሰሙበት ወደዚያ አመጧቸው፡፡
\s5
\v 56 በየትኛውም እርሱ በገባባቸው መንደሮች ወይም ከተማዎች ወይም ሀገሮች ህሙማንን በገበያ ሥፍራዎች ያስቀምጧቸው፣ ቢቻላቸው ሊዳስሱት ካልሆነም የልብሱን ጫፍ ለመንካት ይለምኑት ነበር፤ የዳሰሱትም ሁሉ ይድኑ ነበር፡፡
\s5
\c 7
\cl ምዕራፍ 7
\p
\v 1 ፈሪሳውያንና ከኢየሩሳሌም የመጡ አንዳንድ ጸሓፍት በአንድ ላይ ተሰብስበው ወደ ኢየሱስ መጡ፡፡
\s5
\v 2 ከደቀመዛሙርቱ አንዳንዶቹ በረከሰ እጅ ማለትም ባልታጠበ እጅ እንጀራ ሲበሉ አዩ፡፡
\v 3 (ፈሪሳውያንና ሁሉም አይሁድ የአባቶችን ወግ ስለሚጠብቁ እጆቻቸውን ካልታጠቡ በቀር አይበሉም ነበር)
\v 4 ከገበያ ስፍራ ሲመጡ እጃቸውን ካልታጠቡ በቀር አይበሉም ነበር ፤እንዲሁም ዋንጫዎችን፣ ማሰሮዎችንና የናስ እቃዎችን ማጠብን የመሳሰሉ ሌሎች በርካታ ወጎችን ይጠብቁ ነበር፡፡
\s5
\v 5 ፈሪሳውያንና ጸሓፍት "ደቀመዛሙርትህ በአባቶች ወግ መሰረት የማይጓዙት፣ ነገር ግን ባልታጠበ እጅ የሚበሉት ለምንድን ነው?" ብለው ጠየቁት ፡፡
\s5
\v 6 እርሱም እንዲህ ሲል መለሰላቸው፡፡ ኢሳይያስ ስለ እናንተ ስለ ግብዞች በተናገረው ትንቢት፣ ይህ ሕዝብ በከንፈሩ ብቻ ያከብረኛል፤ ልቡ ግን ከእኔ በጣም የራቀ ነው፤
\v 7 ሰው ሠራሽ ሥርዐት እያስተማሩ በከንቱ ያመልኩኛል˝ ተብሎ የተጻፈው ትክክል ነው፡፡
\s5
\v 8 እናንተ የእግዚአብሔርን ሕግ ትታችሁ የሰዎችን ወግ ታጠብቃላችሁ፡፡
\v 9 እንዲህም አላቸው፡፡ ወጋችሁን ለመጠበቅ ስትሉ የእግዚአብሔርን ሕግ ትሽራላችሁ፡፡
\v 10 ሙሴ፣ «አባትህንና እናትህን አክብር፤ አባቱን ወይም እናቱን የሚሳደብ ሞትን ይሙት» ብሏልና፡፡
\s5
\v 11 እናንተ ግን አንድ ሰው እናቱን ወይም አባቱን፣ «ከእኔ ልታገኙ የሚገባችሁን እርዳታ ቁርባን አድርጌዋለሁ፤ ማለትም ለእግዚአብሔር ሰጥቼዋለሁ» ቢላቸው፣
\v 12 ከዚህ በኋላ ለአባቱና ለእናቱ ምንም ነገር እንዲያደርግ አትፈቅዱለትም፡፡ ለሌሎች በምታስተላልፉት ወግ የእግዚአብሔርን ቃል ትሽራላችሁ፡፡
\v 13 ይህን የመሳሰሉ ብዙ ነገሮችንም ታደርጋላችሁ፡፡
\s5
\v 14 ደግሞም ሕዝቡን ወደ እርሱ ጠርቶ እንዲህ አላቸው፣ ሁላችሁም ስሙኝ ፤ አስተውሉም፡፡
\v 15 ከውጭ ወደ ውስጡ ገብቶ ሰውን የሚያረክስ ምንም ነገር የለም፡፡
\v 16 ነገር ግን ከውስጡ የሚወጡ ነገሮች እነርሱ ሰውን ያረክሱታል፡፡
\s5
\v 17 ከሕዝቡ ተለይቶ ወደ ቤት እንደ ገባም ደቀመዛሙርቱ ስለ ምሳሌው ጠየቁት፡፡
\v 18 እርሱም፣ «እናንተም አልተረዳችሁምን? ከውጭ ወደ ውስጡ ገብቶ ሰውን የሚያረክሰው ምንም ነገር እንደሌለ አታስተውሉምን?» አላቸው፡፡
\v 19 ምክንያቱም ፣ወደ ውስጡ (ዐፉ) የሚገባው ነገር ወደ ሆዱ እንጂ ወደ ልቡ የሚገባ ስላልሆነ ከሰውነቱ የሚወጣ አይደለምን? ይህን በማለቱ ምግብ ሁሉ ንጹሕ መሆኑን ተናገረ፡፡
\s5
\v 20 20እንዲህም አለ፤ ከሰው የሚወጣ ያ ሰውን ያረክሰዋል፡፡
\v 21 ከውስጥ ከሰው ልብ ክፉ ሐሳብ፣ ዝሙት፣ መስረቅ፣ መግደል፣
\v 22 ምንዝር፣ ስግብግብነት፣ ክፋት፣ ማታለል፣ መዳራት፣ ምቀኝነት፣ ስም ማጥፋት፣ ትእቢት፣ ስንፍና ይወጣሉ፡፡
\v 23 እነዚህ ክፉ ነገሮች ሁሉ ከውስጥ ይወጣሉ፡ ሰውንም ያረክሱታል፡፡
\s5
\v 24 ከዚያም ተነሥቶ ወደ ጢሮስና ሲዶና አካባቢ ሄደ፡፡ ያለበትን ማንም እንዳያውቅም ወደ አንድ ቤት ገባ ፤ሆኖም ሊደበቅ አልቻለም፡፡
\v 25 ወዲያውኑም ስለ እርሱ የሰማችና ትንሽ ልጅዋ በእርኩስ መንፈስ የተያዘችባት አንዲት ሴት ወደ እርሱ መጥታ በእግሩ ሥር ተደፋች፡፡
\v 26 ሴቲቱ ዝርያዋ ከሲሮፊኒቃዊት ወገን የሆነ ግሪካዊት ነበረች፡፡ እርስዋም ኢየሱስ በልጅዋ ውስጥ ያለውን ጋኔን እንዲያወጣላት ለመነቸው፡፡
\s5
\v 27 እርሱም «በመጀመሪያ ልጆች ይጥገቡ፤ የልጆችን እንጀራ ወስዶ ለውሾች መስጠት ተገቢ አይደለምና» አላት፡፡
\v 28 እርስዋ ግን «አዎን ጌታ ሆይ፤ ውሾችም እኮ ከገበታ ሥር የሚወዳድቀውን የልጆችን ፍርፋሪ ይበላሉ፡፡» ብላ መለሰችለት፡፡
\s5
\v 29 ኢየሱስም ፣ እንዲህ በማለትሽ ወደ ቤትሽ ሂጂ ጋኔኑ ከልጅሽ ወጥቷል አላት፡፡
\v 30 ወደ ቤትዋም ሄደች፤ልጅዋም አጋንንቱ ለቅቋት ዐልጋው ላይ ተኝታ አገኘቻት፡፡
\s5
\v 31 ደግሞም ከጢሮስ አካባቢ ተነሥቶ በሲዶና በኩል አድርጎ በዐሥሩ ከተሞች ዐልፎ ወደ ገሊላ ባሕር መጣ፡፡
\v 32 እጁን እንዲጭንበትና እንዲፈውሰው አንድ መስማት የተሳነውና ኮልታፋ ሰው ወደ እርሱ አመጡ፡፡
\s5
\v 33 እርሱም ከሕዝቡ ለይቶ ወደ ገለልተኛ ስፍራ ወሰደው፤ጣቶቹን በጆሮዎቹ ውስጥ አስገብቶ እንትፍ አለበት፤ምላሱንም ነካው፡፡
\v 34 ወደ ሰማይ ቀና ብሎ ተመለከተና በረጅሙ ተንፍሶ «ኤፍታህ» አለው፡፡ ይህም ተከፈት ማለት ነው፡፡
\v 35 ጆሮዎቹ ተከፈቱ፤ የታሰረውም ምላሱ ተፈታ፡፡ ጥርት አድርጎም ተናገረ፡፡
\s5
\v 36 ኢየሱስም ይህን ለማንም እንዳይናገሩ አዘዛቸው፤ ሆኖም አጥብቆ ባዘዛቸው መጠን አብልጠው አሰራጩት ፡፡
\v 37 እነርሱም ከልክ በላይ ተደንቀው ፣ ሁሉንም ነገር ደኅና አድርጓል፤እርሱ መስማት የተሣነው እንዲሰማ ኮልታፋውም እንኳ እንዲናገር ያደርጋል አሉ፡፡
\s5
\c 8
\cl ምዕራፍ 8
\p
\v 1 በእነዚያ ቀናት እንደገና ብዙ ህዝብ በተሰበሰበና የሚበሉት ባጡ ጊዜ
\v 2 ኢየሱስም ደቀመዛሙርቱን ወደእርሱ ጠርቶ ህዝቡ ከኔ ጋር ሶስት ቀናት ቆይተዋል የሚበሉትም የላቸውምና እራራላቸዋለሁ
\v 3 ሳይበሉ ብሰዳቸውም በመንገድ ላይ ይደክማሉ አንዳንዶቹም ከሩቅ ሥፍራ ነው የመጡት አላቸው፡፡
\v 4 ደቀመዛሙርቱም በዚህ ምድረበዳ እነዚህን ሁሉ የሚያጠግብ እንጀራ እንዴት ይገኛል ብለው መለሱለት፡፡
\s5
\v 5 ስንት እንጀራ አላችሁ ብሎ ጠየቃቸው፡፡ ሰባት አሉት ፤
\v 6 ህዘቡን በምድር ላይ እንዲቀመጡ አዘዘ ሰባቱንም እንጀራ ተቀብሎ እግዚአብሔርን ካመሰገነ በኋላ ቆርሶ እንዲያቀርቡላቸው ለደቀመዛሙርቱ ሰጣቸው እነርሱም ለህዝቡ አቀረቡላቸው፡፤
\s5
\v 7 ጥቂትም ትናንሽ አሦች ነበሯቸው ባርኮም ያንንም አንዲያቀርቡላቸው አዘዘ፡፡
\v 8 ሕዝቡም በልተውም ጠገቡ፡ ደቀመዛሙርቱም የተረፈውን ቁርስራሽ ሰባት ታላላቅ መሶብ አነሱ፡፡
\v 9 የህዝቡም ቁጥር ቁጥራቸውም አራት ሺ ያህል ነበር፡፡ ከዚያም ኢየሱስ ህዝቡን አሰናበታቸው ፡፡
\v 10 ወዲያውም ከደቀመዛሙርቱ ጋር ወደ ጀልባ ገብተው ወደ ዳልማኑታ አውራጃ አካባቢ ሄዱ፡፡
\s5
\v 11 ፈሪሳውያንም ወደ ኢየሱስ እርሱ መጥተው ከእግዚአብሔር ዘንድ የሆነ ምልክትን እንዲያሳያቸው በመፈለግ ሊፈትኑት ይጠይቁት ጀምር፡፡
\v 12 ኢየሱስም እርሱም በመንፈሱ እጅግ ተበሳጭቶ በዚህ ዘመን ያለ ህዝብ ለምን ምልክት ይፈልጋል እዉነት እላችኋለሁ እናንተ ሰዎች አይሰጣችሁም አላቸው፡፡
\v 13 ትቶአቸው እንደገና ወደ ጀልባ ገብቶ ወደ ባህሩ ማዶ ተሻገረ፡፡
\s5
\v 14 ደቀመዛሙርቱም እንጀራ መያዝን ረሱ፡፡
\v 15 በጀልባ ውስጥም ከአንድ እንጀራ በቀር ምንም አልያዙም ነበር።
\s5
\v 16 ኢየሱስ ከፈሪሳዊያንና ከንጉሥ ሄሮድስ እርሾ ተጠንቀቁ ብሎ አሳሰባቸው፡፡ እንጀራ ስላልያዝን ነው ብለው እርስ በእርሳቸው ተነጋገሩ ፡፡
\v 17 ኢየሱስም ይህን አውቆ እንጀራ ስለሌላችሁ ለምን ትነጋገራላችሁ፡፡ እስከአሁን አልገባችሁምን ወይም እስከአሁን አታስተውሉምን ልባችሁ ደንዝዞአልን
\s5
\v 18 አይን እያላችሁ አታዩምን ጆሮ እያላችሁ አትሰሙምን አታስታውሱምን
\v 19 አምስቱን እንጀራ ለአምስት ሺ ባካፈልኩ ጊዜ ስንት መሶብ ቁርስራሽ ሰበሰባችሁ ብሎ ጠየቃቸው እነርሱም አሥራ ሁለት ብለው መለሱለት፡፡
\s5
\v 20 ሰባቱን ለአራት ሺ ባካፈልኩ ጊዜስ ስንት ቅርጫት ቁርስራሽ አነሳችሁ አላቸው ሰባት አሉት ፡፡
\v 21 ገና አታስተውሉምን አላቸው፡፡
\s5
\v 22 ወደ ቤተ ሳይዳም መጡ፡፡ የአካባቢው ሰዎችም አይነ ስውር የሆነን ሰው ወደ እርሱ አምጥተው እንዲዳስሰው ለመኑት፡፡
\v 23 የአይነስውሩንም ሰው እጅ ይዞ ከመንደሩ ውጭ ወሰደው፡፡ በአይኖቹም ላይ እንትፍ ብሎና እጁን ጭኖ አሁን ይታይሀልን ብሎ ጠየቀው፡፡
\s5
\v 24 ቀና ብሎ ተመለከተና ሰዎች ሲራመዱ እንደዛፍ ሆነው ይታየኛል አለው፡፡
\v 25 እንደገናም እጁን በአይኑ ላይ በጫነበት ጊዜ በሚገባ ተመለከተ የአይኑም ብርሀን ተመለሰለት ሁሉንም ነገር አጥርቶ አየ፡፡
\v 26 ኢየሱስም ወደ መንደሩ እንኳ እንዳትገባ ብሎ ወደ ቤቱ አሰናበተው፡፡
\s5
\v 27 ኢየሱስም ከደቀመዛሙርቱ ጋር ወደ ፊሊጶስፕ ቂሳሪያ ዙሪያ ወዳሉ መንደርሮች ሄዱ፡ በመንገድም ላይ ሳሉ ሰዎች እኔን ማነው ይላሉ ብሎ ጠየቃቸው
\v 28 እነርሱም መጥምቁ ዮሐንስ ሌሎች ደግሞ ኤልያስ አንዳንች ግን ከነቢያት አንዱ ብለው መለሱለት፡፡
\s5
\v 29 እንደገናም እናንተስ እኔ ማን እንደሆንኩ ትላለችሁ ብሎ ጠየቃቸው፡፡ ጴጥሮስም አንተ መሲሁ ነህ በማለት መለሰለት፡፡
\v 30 ስለእርሱ ለማንም እንዳይናገሩ አስጠነቀቃቸው፡፡
\s5
\v 31 የሰው ልጅ ብዙ መከራ እንደሚቀበል በሽማግሌዎች፣ በካህናት አለቆችና በጻፎች እንደሚነቀፍና እንደሚገደል በሦስተኛውም ቀን እንደገና እንደሚነሳ እንዳለው ያስተምራቸው ጀመር፡፡
\v 32 ይህንንም በግልጽ ተናገረ፡፡ ጴጥሮስም ወስዶ ሊገስጸው ጀመረ፡፡
\s5
\v 33 ኢየሱስም ዞር ብሎ ደቀመዛሙርቱን አየና ወደ ኋላዬ ሂድ አንተ ሰይጣን የሰውን እንጂ የእግዚአብሔርን ነገር አታስብምና ብሎ ጴጥሮስን ገሰጸው፡፡
\v 34 ህዘቡንና ደቀመዛሙርቱንም ወደ እርሱ ጠርቶ ሊከተለኝ የሚወድ ማንም ቢኖር ራሱን ይካድ መስቀሉንም ተሸክሞ ይከተለኝ፡፡
\s5
\v 35 ህይወቱን ሊያድን የሚወድ ሁሉ ያጠጣፋታልና ነፍሱን ግን ስለኔ ወይም ስለወንጌል የሚያጣ ያገኛታልና፡፡
\v 36 ሰው ዓለምን ሁሉ ቢያተርፍ ነፍሱን ግን ቢያጣ ምን ይጠቅመዋል፡፡
\v 37 ወይስ ሰው ስለነፍሱ ቤዛ ምን ይሰጣል፡፡
\s5
\v 38 በዚህ አመንዝራ ኃጢአተኛ ህዝብ ፊት በእኔና በቃሌ የሚያፍርብኝ ማንም ቢኖር የሰው ልጅም ከቅዱሳን መላዕክቱ ጋር በአባቱ ክብር በሚመጣበት ጊዜ ያፍርበታል፡፡
\s5
\c 9
\cl ምዕራፍ 9
\p
\v 1 ኢየሱስም እውነት እላችኋለሁ፣ በዚህ ከቆሙት አንዳንዶቹ የእግዚአብሔር መንግሥት በኃይል መምጣቷን ሳያዩ የማይሞቱ አሉ አላቸው፡፡
\v 2 ከስድስት ቀን በኋላም ኢየሱስ ጴጥሮስን፣ ያዕቆብንና ዮሐንስን ለብቻቸው ይዞ ወደ ረጅም ተራራ ላይ አመጣቸው፡፡
\v 3 በፊታቸውም ተለወጠባቸው፤ ልብሱም አጣቢ በምድር ላይ ሊያነጻው እስከማይችል ድረስ ተብለጭልጮ ነጭ ሆነ፡፡
\s5
\v 4 ሙሴና ኤልያስ ታዩአቸው፤ ከኢየሱስ ጋርም ይነጋገሩ ነበር፡፡
\v 5 ጴጥሮስም መልሶ ኢየሱስን ረቡኒ! በዚህ መሆን ለእኛ መልካም ነው፤ አንድ ለአንተ፣ አንድ ለሙሴና አንድ ለኤልያስ ሦስት ዳሶችን እንሥራ አለው፡፡
\v 6 እጅግ ፈርተው ስለነበረ የሚመልሰውን አያውቅም ነበር፡፡
\s5
\v 7 ከዚያም ደመና መጥቶ ጋረዳቸው፤ ከደመናውም ውስጥ በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው፣ እርሱን ስሙት የሚል ድምፅ መጣ፡፡
\v 8 ድንገት ዙሪያቸውን ሲመለከቱ ከኢየሱስ በቀር ከእነርሱ ጋር ሌላ ማንንም አላዩም፡፡
\s5
\v 9 ከተራራው ሲወርዱ ሳሉም ይህንን ያዩትን ነገር ሁሉ የሰው ልጅ ከሙታን እስኪነሳ ድረስ ለማንም እንዳይናገሩ አዘዛቸው፡፡
\v 10 እነርሱም ቃሉን ይዘው ከሙታን መነሳት ማለት ምን ማለት ነው ተባባሉ፡፡
\s5
\v 11 እነርሱም ጸሐፍት አስቀድሞ ኤልያስ መምጣት አለበት የሚሉት ለምንድነው ብለው ጠየቁት፡፡
\v 12 ኢየሱስም ኤልያስማ በርግጥ አስቀድሞ ይመጣል፤ ሁሉንም ነገር ያስተካክላል፡፡ ስለ ሰው ልጅ ብዙ መከራ እንዲቀበልና እንዲጣል የተጻፈው ታዲያ እንዴት ይሆናል?
\v 13 እኔ ግን እላችኋለሁ! ኤልያስ መጥቷል፤ ስለ እርሱም አንደተጻፈው የወደዱትን አደረጉበት፡፡
\s5
\v 14 ወደ ደቀመዛሙርቱ በመጡ ጊዜ ብዙ ሕዝብ ከበዋቸው ጸሓፍትም ሲጠይቋቸው ተመለከቱ፡፡
\v 15 ወዲያው ሕዝቡ ሁሉ ኢየሱስን ባዩት ጊዜ እጅግ ተገርመው ወደ እርሱ በመሮጥ ሰላምታ ሰጡት፡፡
\v 16 እርሱም ስለምንድነው የምትጠይቋቸው? ብሎ ጠየቃቸው፡፡
\s5
\v 17 ከሕዝቡም መሐል አንዱ መምህር ሆይ! ዲዳ መንፈስ ያደረበትን ልጄን ወዳንተ አመጣሁት፡፡
\v 18 በሚወስደው ቦታ ሁሉ ይጥለውና አረፋ ያስደፍቀዋል፣ ጥርሱን ያንቀጫቅጭና ያደርቀዋል፡፡ እንዲያወጡት ደቀመዛሙርትህን ጠየቅኳቸው፣ እነርሱም አልቻሉም፡፡
\v 19 ኢየሱስም መልሶ እናንተ የማታምኑ ትውልዶች እስከ መቼ ከእናንተ ጋር እኖራለሁ? እስከ መቼስ እታገሳችኋለሁ? ወደ እኔ አምጡት አላቸው፡፡
\s5
\v 20 ወደ እርሱም አመጡለት፤ ባየውም ጊዜ ወዲያው መንፈሱ በምድር ላይ በኃይል ጥሎ እያንፈራገጠ አረፋ አስደፈቀው፡፡
\v 21 ኢየሱስም የልጁን አባት ይህ ከያዘው ምን ያህል ጊዜ ሆነው? ሲል ጠየቀው፡፡ እርሱም ከሕጻንነቱ ጀምሮ ነው፡፡
\v 22 ብዙ ጊዜ ሊያጠፋው በውሃና በእሳት ላይ ይጥለዋል፤ የሚቻልህ ከሆነ እዘንልንና እርዳን አለው፡፡
\s5
\v 23 ኢየሱስም የሚቻልህ ከሆነ አልክን ለሚያምን ሁሉም ነገር ይቻላል አለው፡፡
\v 24 ወዲያው የልጁ አባት ጮኸና አምናለሁ፣ እንዳምንም እርዳኝ አለው፡፡
\v 25 ኢየሱስ ሕዝቡ እየሮጠ ሲመጣ ተመልክቶ እርኩሱን መንፈስ አንተ ዲዳ ደንቆሮም መንፈስ ከእርሱ እንድትወጣ ተመልሰህም እንዳትገባበት አዝሃለሁ ብሎ ገሰጸው፡፡
\s5
\v 26 መንፈሱም ካንፈራገጠው በኋላ ጮኾ ወጣ፡፡ ብዙዎች ሞተ እስኪሉ ድረስም እንደ ሞተ ሰው ሆነ፡፡
\v 27 ኢየሱስ ግን እጁን ይዞ አስነሳው፤ እርሱም ተነሣ፡፡
\s5
\v 28 ወደ ቤት በገቡ ጊዜም ደቀመዛሙርቱ እኛ ልናስወጣው ያልቻልነው ለምንድነው? ብለው ለብቻው ጠየቁት፡፡
\v 29 ኢየሱስም እንዲህ ዓይነቱ ወገን በጸሎት ካልሆነ በስተቀር አይወጣም አላቸው፡፡
\s5
\v 30 ከዚያም ወጥተው በገሊላ በኩል አለፉ፤ በዚያ መሆኑን ማንም እንዲያውቅ አይፈልግም ነበር፡፡
\v 31 ደቀመዛሙርቱንም እንዲህ ሲል አስተማራቸው፤ የሰው ልጅ በሰዎች እጅ ታልፎ ይሰጣል፣ ይገድሉታልም፣ ከተገደለ ከሶስት ቀን በኋላም ይነሣል አላቸው፡፡
\v 32 ነገር ግን የተናገራቸውን አላስተዋሉም፤ እንዳይጠይቁትም ፈርተው ነበር፡፡
\s5
\v 33 ወደ ቅፍርናሆም መጡ፤ በቤት ሳሉም መንገድ ላይ ስለምን ጉዳይ ነበር የምትነጋገሩት ብሎ ደቀመዛሙርቱን ጠየቃቸው፡፡
\v 34 ከእነርሱ ማን ይበልጥ እንደሆነ ተከራክረው ነበርና ዝም አሉ፡፡
\v 35 ተቀምጦም አሥራ ሁለቱን ጠራቸው፣ እንዲህም አላቸው፣ ከእናንተ የመጀመሪያ ሊሆን የሚወድ የሁሉ መጨረሻና አገልጋይ ይሁን፤
\s5
\v 36 ትንሽ ልጅ በመካከላቸው አቁሞና አቅፎት እንዲህ አላቸው፤
\v 37 ማንም እንደዚህ ካሉት ታናናሽ ልጆች አንዱን በስሜ የሚቀበል እኔን ይቀበላል፣ እኔንም የሚቀበል የሚቀበለው የላከኝን ነው እንጂ እኔን አይደለም፡፡
\s5
\v 38 ዮሐንስም መምህር ሆይ! አንድ ሰው በስምህ አጋንንትን ሲያስወጣ አየነው፤ ስለማይከተለንም ከለከልነው አለው፡፡
\v 39 ኢየሱስ ግን በስሜ ተአምራትን አድርጎ ፈጥኖ በእኔ ላይ ክፉ ሊናገር የሚችል የለምና አትከልክሉት፤
\s5
\v 40 የማይቃወመን ሁሉ ከእኛ ጋር ነው አለው፡፡
\v 41 እውነት እላችኋለሁ የክርስቶስ በመሆናችሁ ምክንያት አንድ ብርጭቆ ውሃ እንድትጠጡ የሚሰጣችሁ ዋጋውን አያጣም፡፡
\s5
\v 42 በእኔ ከሚያምኑ ከእነዚህ ከታናናሾቹ አንዱን ከእምነቱ የሚያስት ሰው ትልቅ የወፍጮ ድንጋይ በአንገቱ ላይ ታሥሮ በጥልቅ ባህር ላይ ቢጣል ይሻለው ነበር፡፡
\v 43 እጅህ ለመሰናከልህ ምክንያት የምትሆን ከሆነ ቆርጠህ ጣላት፤ ሁለት እጅ ኖሮህ እሳቱ ወደማይጠፋበት ወደ ሲዖል ከምትሔድ አካልህ ጎሎ ወደ ሕይወት ብትገባ ይሻልሃልና፡፡
\v 44
\s5
\v 45 እግርህ ለመሰናከልህ ምክንያት የሚሆን ከሆነ ቆርጠህ ጣለው፤ ሁለት እግር ኖሮህ ወደ ሲዖል ወደ እሳቱ ከምትጣል አንድ እግር ኖሮህ ወደ ሕይወት ብትገባ ይሻልሃል፡፡
\v 46
\s5
\v 47 ዐይንህ ለመሰናከልህ ምክንያት የምትሆን ከሆነ አውጥተህ ጣላት፤
\v 48 ሁለት ዐይን ኖሮህ ትሉ ወደማይሞትበት፣ እሳቱ ወደማይጠፋበት ከምትገባ አንድ ዐይና ሆነህ ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ብትገባ ይሻልሃል፡፡
\s5
\v 49 እያንዳንዱ ሰው በእሳት ይቀመማል፡፡
\v 50 ጨው መልካም ነው፤ የጨውነት ጣዕሙን ቢያጣ ግን ምን ታደርጉታላችሁ? በእያንዳንዳችሁ ሕይወት የጨውነት ጣዕም ይኑርባችሁ! እርስ በርሳችሁም በሰላም ኑሩ፡፡
\s5
\c 10
\cl ምዕራፍ 10
\p
\v 1 ኢየሱስም ከዚያ ተነስቶ ከዮርዳኖስ ወንዝ ማዶ ወደ ይሁዳ አውራጃዎች መጣ፡፡ ብዙ ህዝብም በአንድ ላይ ሆነው እንደገና ወደ እርሱ መጡ፡፡ እንደልማዱም ያስተምራቸው ጀመር፡፡
\v 2 ፊሪሳውያንም ወደ ኢየሱስ መጥተው ሊፈትኑት አንድ ሰው ሚስቱን መፍታት ተፈቅዶለታል ሲሉ ጠየቁት፡፡
\v 3 እርሱም መልሶ ሙሴ ምን ብሎ አዘዛችሁ አላቸው፡፡
\v 4 እነርሱም የፍቺውን ጽፈት ሰጥቶ ይፍታት ብሎ ደንግጓል አሉት፡፡
\s5
\v 5 ኢየሱስ ግን ሙሴ ስለልባችሁ ድንዛዜ ይህን ትዕዛዝ ሰጣችሁ እንጂ
\v 6 ከፍጥረት መጀመሪያ ግን እግዚአብሔር ወንድና ሴት አድርጎ ፈጠራቸው፡፡
\s5
\v 7 በዚህም ምክንያት ሰው እናቱንና አባቱን ይተዋል ከሚስቱም ጋር ይጣበቃል
\v 8 ሁለቱም አንድ ስጋ ይሆናሉ ስለዚህም አንድ ሥጋ እንጂ ከእንግዲህ ሁለት አይደሉም
\v 9 እንግዲህ እግዚአብሔር ያጣመረውን ሰው አይለየው አላቸው፡፡
\s5
\v 10 በቤትም ሳሉ ደቀመዛሙርቱ ስለጉዳዩ እንደገና ጠየቁት፡፡
\v 11 ኢየሱስም ማንም ሚስቱን ፈቶ ሌላይቱን ቢያገባ በሚስቱ ላይ ያመነዝራል፡፡
\v 12 እንዲሁም እርሷም ራሷ ባሉዋን ትታ ሌላ ሰው ካገባች ታመነዝራለች አላቸው ፡፡
\s5
\v 13 ህዝቡም እንዲዳስሳቸው ህጻናትን ወደ ኢየሱስ ያመጡ ነበር፡፡ ደቀመዛሙርትም ገሰጹዋቸው፡፡
\v 14 ኢየሱስ ግን ባየ ጊዜ በቁጣ ተሞልቶ ህጻናትን ወደ እኔ ይመጡ ዘንድ ተው አትከልክሏቸው፡፡ የእግዚአብሔር መንግሥት እንደነዚህ ላሉት ናትና አላቸው፡፡
\s5
\v 15 እውነት እላችኋለሁ የእግዚአብሔርን መንግሥት እንደ ህጻን ሆኖ የማይቀበላት ሊገባባት አይችልም፡፡
\v 16 ህጻናቱንም አቅፎ እጁን ጭኖ ባረካቸው፡፡
\s5
\v 17 በመንገድም ሳሉ አንድ ሰው ወደእርሱ ሮጠና በፊቱ ተንበርክኮ ቸር መመህር ሆይ የዘላለምን ህይወት እንድወርስ ምን ማድረግ ይገባኛል? ብሎ ጠየቀው ፡፡
\v 18 ኢየሱስም ለምን ቸር ትለኛለህ ከአንዱ ከእግዚአብሔር በቀር ቸር የለም አለው፡፡
\v 19 ትዕዘዛትን ታወቃለህ አትግደል አትስረቅ አታመንዘር በሀሰት አትመስክር አታታልል አባትህንና እናትህን አክብር አለው፡፡
\s5
\v 20 እርሱም መምህር ሆይ እነኚህን ሁሉ ከልጅነቴ ጀምሮ ጠብቄአለሁ አለው፡፡
\v 21 ኢየሱስም አይቶ ወደደውና አንዲት ነገር ቀርታሀለች ሂድ ያለህን ሁሉ ሽጥና ለድሆች ስጥ መዝገብም በሰማይ ይቆይሀል መጥተህም ተከተለኝ አለው፡፡
\v 22 እርሱም ብዙ ሀብት ነበረውና በሰማው ነገር ፊቱ ተቁሮ እያዘነ ሄደ፡፡
\s5
\v 23 ኢየሱስም ዙሪያውን ተመለከተና ደቀመዛሙርቱን ለሀብታሞች ወደ እግዚአብሔር መንግሥት መግባት እንዴት ጭንቅ ነው አላቸው፡፡
\v 24 ደቀመዛሙርቱም በንግግሩ እጅግ ተገረሙ፡፡ ኢየሱስ እርሱ ግን መልሶ ልጆች ሆይ በሀብታቸው ለሚታመኑ ወደ እግዚአብሔር መንግስት መግባት እንዴት ከባድ ነው አላቸው፡፡
\v 25 ሀብታም ሰው ወደ መንግስተ ሰማያት ከሚገባ ግመል በመርፌ ቀዳዳ ቢሾልክ ይቀላል አላቸው፡፡
\s5
\v 26 ደቀመዛሙርቱም እጅግ ተገርመው እንግዲያውስ ማን ሊድን ይችላል አሉት፡፡
\v 27 ኢየሱስም ወደ እነርሱ ተመከተና ለሰዎች ይህ አይቻልም ነገር ግን ለእግዚአብሔር ይቻላል ለእግዚአብሔር ሁሉ ይቻላልና አላቸው፡፡
\v 28 ጴጥሮስም ጌታ ሆይ እኛ ሀሉን ትተን ተከልንህ ይለው ጀመር፡፡
\s5
\v 29 ኢየሱስም እውነት እላችኋለሁ ስለኔና ስለ ወንጌል ቤቱን ወንዱሞቹን ወይም እህቶቹንወይም እናቱን ወይም አባቱን ወይም ልጆቹን ወይም መሬቱን የሚተው
\v 30 በዚህ ዓለም መቶ እጥፍ ቤቶችን ወንድሞችን እህቶችን እናቶችን ልጆችንና መሬት ከስደት ጋር በሚመጣውም አለም የዘላለምን ህይወት የማይቀበል የለም
\v 31 ነገር ግን ብዙዎች ፊተኞች ኋለኞች ኋለኞችም ፊተኞች ይሆናሉ አላቸው፡፡
\s5
\v 32 ወደ ኢየሩሳሌም ሲሄዱ ሳለ ኢየሱስ ከፊት ከፊታቸው ይሄድ ነበር፡፡ እጅግም ተገርመው ነበር የሚከተሉትም በጣም ፈርተው ነበር፡፡ አስራሁለቱን እንደገና ወስዶ ሊደርስበት ያለውን ነገር ይነግራቸው ጀመር፡፡
\v 33 እነሆ ወደ ኢየሩሳሌም እንሄዳለን የሰው ልጅም ለካህናት አለቆችና ለጻፎች አልፎ ይሰጣል እነርሱም ሞትን ይፈርዱበታል ለአህዛብም አሳልፈው ይሰጡታል፡፡
\v 34 አህዛብም/ፈሪሳዊያን ይቀልዱበታል ይተፉበታል ይገርፉታል ይገድሉታልም ከሶስት ቀን በኋላም ይነሳል እያለ ይነግራቸው ጀመር፡፡
\s5
\v 35 የዘብድዮስ ልጆች ያዕቆብና ዮሀንስ ወደ ኢየሱስ ቀርበው መምህር ሆይ የምንጠይቅህን ሁሉ እንድታደርግልን እንለምንሀለን አሉት፡፡
\v 36 እርሱም ምን እንዳደርግላችሁ ትፈልጋለችሁ አላቸው፡፡
\v 37 እነርሱም በክብርህ በምትሆንበት ጊዜ አንዳችን በቀኝህ አንዳችን በግራህ እንድንቀመጥ ፍቀድ አሉት፡፡
\s5
\v 38 ኢየሱስ ግን የምትለምኑትን አታውቁም እኔ የምጠጣውን ጽዋ ልትጠጡ እኔ የምጠመቀውን ጥምቀት ልትጠመቁ ትችላላችሁን አላቸው፡፤
\v 39 እነርሱም እንችላለን አሉት፡፡ ኢየሱስም እኔ የምጠጣውን ጽዋ ትጠጣላችሁ እኔ የምጠመቀውን ጥምቀት ትጠመቃላችሁ
\v 40 ነገር ግን በግራዬና በቀኜ መሆን ለተዘጋጀላቸው ነው እንጂ እኔ የምሰጠው አይደለም አላቸው፡፡
\s5
\v 41 አሥሩ ደቀማዘሙርትም ይህን በሰሙ ጊዜ በያዕቆብና በዮሀንስ ላይ ተቆጡ፡፡
\v 42 ኢየሱስም ወደ እርሱ ጠርቶ የአህዛብ አለቆች በሚመሩዋቸው ላይ እንደሚሠለጥኑባቸው ታላላቆቻቸውም እንደሚገዙዋቸው ታውቃላችሁ፡፡
\s5
\v 43 በእናንተ ዘንድ ግን እንዲህ አይደለም ነገር ግን ከእናንተ ማንም የበላይ(ታላቅ) ለመሆን የሚፈልግ የሁሉ አገልጋይ ይሁን
\v 44 ፊተኛ ለመሆን የሚፈልግም የሁሉ ባሪያ ይሁን
\v 45 የሰው ልጅም ሊያገለግል ነፍሱንም ለብዙዎች ቤዛ ሊያደርግ እንጂ እንዲያገልግሉት አልመጣም አላቸው፡፡
\s5
\v 46 ኢየሱስና ደቀመዛሙርቱም ወደ ኢያሪኮ መጡ፡፡ ከደቀመዛሙርቱና ከብዙ ህዝብ ጋር ከኢያሪኮ በመውጣት ላይ ሳለ የጤሚዮስ ልጅ ዓይነ ስወሩ ለማኝ በርጠሚዮስ በመንገድ ዳር ተቀምጦ ይለምን ነበር፡፡
\v 47 የናዝሬቱ ኢየሱስ እያለፈ መሆኑን ሲሰማ የዳዊተ ልጅ ኢየሱስ ሆይ እራራልኝ እያለ ጮኸ፡፡
\v 48 ብዙዎችም ዝም እንዲል ገሰፁት፡፡ እርሱ ግን አብዝቶ የዳዊት ልጅ ሆይ እራራልኝ ብሎ ጮኸ፡፡
\s5
\v 49 ኢየሱስም ቆመና ጥሩት አለ፡፡ እነርሱም አይዞህ መምህሩ ይጠራሀልና ተነሳ አሉት፡፡
\v 50 በርጠሚዮስም ልብሱን ጥሎ እየዘለለ ወደ ኢየሱስ መጣ፡፡
\s5
\v 51 ኢየሱስም ምን እንዳደርገልህ ትወዳለህ አለው፡፡ ዓይነ ስውሩም ሰው መምህር ሆይ ማየት እንድችል አለው፡፡
\v 52 ኢየሱስም መንገድህን ሂድ እምነትህ አድኖሀል አለው፡፡ ወዲያውም አየ ኢየሱስንም ተከትሎ ሄደ፡፡
\s5
\c 11
\cl ምዕራፍ 11
\p
\v 1 ከደብረ ዘይት ተራራ ወደ ኢየሩሳሌም፣ ወደ ቤተ ፋጌና ወደ ቢታንያ በቀረቡ ጊዜ ኢየሱስ ከደቀመዛሙርቱ ሁለቱን ላካቸው፡፡
\v 2 እንዲህም አላቸው፣ ፊት ለፊታችን ወዳለው መንደር ሂዱ፤ወዲያው እንደ ገባችሁም ማንም ሰው ተቀምጦበት የማያውቅ ውርንጫ መንገድ ዳር ታስሮ ታገኛላችሁ፡፡ ፍቱትና አምጡልኝ፤
\v 3 ማንም ለምን ይህን ታደርጋላችሁ ቢላችሁ ለጌታ ያስፈልገዋል በሉት፤ እርሱም ይለቅቀዋል አላቸው፡፡
\s5
\v 4 እነርሱም ሄዱ፤ አንድ ውርንጫ ከቤት ውጭ በመንገድ ዳር ታስሮ አገኙ፤ ፈቱትም፡፡
\v 5 በአካባቢው ከቆሙት አንዳንዶቹ ሰዎች ለምን ፈታችሁት? አሏቸው፡፡
\v 6 እነርሱም ልክ ኢየሱስ እንዳላቸው ነገሯቸው፤ ለቀቋቸውም፡፡
\s5
\v 7 ደቀመዛሙርቱም ውርንጫውን ወደ ኢየሱስ አመጡት፤ ልብሳቸውንም አለበሱት፤ ኢየሱስም ተቀመጠበት፡፡
\v 8 ብዙ ሰዎችም ልብሳቸውን ፣ሌሎችም ከየቦታው ቅርንጫፎችን ቆርጠው በሚሄድበት መንገድ ላይ አነጠፉ፡፡
\v 9 ከፊት የቀደሙት ከኋላውም የተከተሉት ሆሳእና! በጌታ ስም የሚመጣ የተባረከ ነው፤
\v 10 የሚመጣው የአባታችን የንጉሥ ዳዊት መንግስት የተባረከ ነው፤ ሆሳእና በአርያም እያሉ ጮኹ፡፡
\s5
\v 11 ኢየሩሳሌም እንደ ደረሰ ወደ ቤተመቅደስ ገባ፡፡ በአካባቢው ያለውን ሁሉ ተመለከተ፤መሽቶም ነበርና ከዐሥራ ሁለቱ ጋር ወደ ቢታንያ ሄደ፡፡
\v 12 በማግስቱም ከቢታንያ እንደ ወጡ ተራበ፤
\s5
\v 13 አንዲት ቅጠሏ ያቆጠቆጠ በለስ ከርቀት አየ፡፡ ምናልባት አንዳች አገኝባት ይሆናል በማለት ወደ እርሷ መጣ፡፡ ሲደርስ ግን በለስ የሚያፈራበት ጊዜ ስላልነበረ ከቅጠል በቀር ምንም አላገኘባትም፡፡
\v 14 ስለዚህም ማንም ሰው ለዘላለም ምንም ፍሬ አያግኝብሽ ብሎ ረገማት፡፡ ደቀመዛሙርቱም ሰሙት፡፡
\s5
\v 15 ወደ ኢየሩሳሌምም እንደ መጡ ወደ ቤተመቅደስ ገባ፤ በዚያም የሚሸጡትንና የሚገዙትን አባረረ፤የገንዘብ ለዋጮችን ጠረጴዛ የርግብ ሻጮችንም መቀመጫቸውን ገለበጠባቸው፡፡
\v 16 ማንም ሰው በቤተ መቅደስ ውስጥ ዕቃ ይዞ እንዳይመላለስ ከለከለ፡፡
\s5
\v 17 አስተማራቸውም፤ ቤቴ የአሕዛብ ሁሉ የጸሎት ቤት ይባላል ተብሎ አልተጻፈምን? እናንተ ግን የወንበዴዎች ዋሻ አደረጋችሁት አላቸው፡፡
\v 18 ሊቀ ካህናቱና ጸሓፍትም፣ይህን ሲናገር ሲሰሙ ሕዝቡ ሁሉ በትምህርቱ ተደንቀው ስለ ተከተሉት ፈርተው ነበርና እንዴት እንደሚገድሉት ማሰብ ጀመሩ፡፡
\v 19 ኢየሱስም በየምሽቱ ከከተማ ይወጣ ነበር፡፡
\s5
\v 20 በማለዳ ሲያልፉም በለሲቱ ከሥሯ ደርቃ አገኟት፡፡
\v 21 ጴጥሮስም አስታውሶ መምህር ሆይ! እነሆ፤የረገምሃት በለስ ደርቃለች አለው፡፡
\s5
\v 22 ኢየሱስም እንዲህ አለው፡፡ በእግዚአብሔር እመን፤
\v 23 እውነት እላችኋለሁ፣ ማንም በልቡ ሳይጠራጠር ይህን ተራራ ከዚህ ተነቅለህ ወደ ባሕር ውስጥ ተወርወር ቢልና የተናገረው እንደሚፈጸም በልቡ ቢያምን ይሆንለታል፡፡
\s5
\v 24 ስለዚህ እላችኋለሁ፤የጸለያችሁትንና የለመናችሁትን ነገር ሁሉ እንደምትቀበሉ ብታምኑ ይሆንላችሁማል፡፡
\v 25 ለጸሎት ስትቆሙ፣ በማንም ላይ ቅርታ ቢኖራችሁ፣ የሰማዩ አባታችሁ ኀጢአታችሁን ይቅር እንዲላችሁ ይቅር በሉ፡፡
\v 26 እናንተ ግን ይቅር ባትሉ በሰማያት ያለው አባታችሁ ደግሞ የቅር አይላችሁም፡፡
\s5
\v 27 በድጋሚም ወደ ኢየሩሳሌም መጡ፡፡ ኢየሱስ ወደ ቤተመቅደስ ሲገባም ሊቀ ካህናት፣ጸሓፍትና ሽማግሌዎችም ወደ ኢየሱስ መጥተው፣
\v 28 እነዚህን ነገሮች የምታደርገው በምን ሥልጣን ነው? ወይም እነዚህን ነገሮች እንድታደርግ ሥልጣን የሰጠህ ማን ነው? አሉት፡፡
\s5
\v 29 ኢየሱስም አንድ ጥያቄ ጠይቃችኋለሁ እናንተም መልሱልኝ፤ እኔም እነዚህን ነገሮች በምን ሥልጣን እንደማደርግ እነግራችኋለሁ አላቸው፡፡
\v 30 መልሱልኝ፤ የዮሐንስ ጥምቀት ከሰማይ ነው? ወይስ ከሰው? አላቸው ፡፡
\s5
\v 31 እነርሱም እርስ በርሳቸው ተመካከሩ፤ ከሰማይ ነው ብንል ታዲያ ለምን አላመናችሁበትም? ይለናል፤
\v 32 ነገር ግን ከሰው ነው ብንል ደግሞ ሰዉ ሁሉ ዮሐንስ ነቢይ ነው ብሎ አምኖበታል ብለው ሕዝቡን ፈሩ፡፡
\v 33 ለኢየሱስም አናውቅም ብለው መለሱለት፡፡ ኢየሱስም እኔም እነዚህን ነገሮች በምን ሥልጣን እንደማደርግ አልነግራችሁም አላቸው፡፡
\s5
\c 12
\cl ምዕራፍ 12
\p
\v 1 ኢየሱስም በምሳሌ ይነግራቸው ጀመር፡፡ አንድ ሰው የወይን ተክል ተከለ፤በዙሪያው ዐጥር ሠራ፤ለወይን መጭመቂያ የሚሆን ጕድጓድ ቈፈረ፤ማማም ሠራ፡፡ ለገበሬዎችም አከራይቶ ወደ ሌላ አገር ሄደ፡፡
\v 2 በወቅቱ የወይኑን ፍሬ እንዲቀበል አንድ አገልጋይ ወደ ገበሬዎቹ ላከ፡፡
\v 3 እነርሱም አገልጋዩን ያዙት፤ ደብድበውም ባዶ እጁን ሰደዱት፡፡
\s5
\v 4 በድጋሚም ሌላ አገልጋይ ላከ፤እነርሱም ፈነከቱት፤ አሳፈሩትም፡፡
\v 5 ሌላም አገልጋይ ወደ እነርሱ ላከ፤ እርሱንም ገደሉት፡፡ ብዙዎች ሌሎችንም ላከ፤ አንዳንዶቹን ደበደቡ፤ ሌሎቹንም ገደሉ፡፡
\s5
\v 6 የወይኑ ተክል ባለቤት አንድ ተወዳጅ ልጅ ነበረው፤ልጄን ያከብሩታል በማለት በመጨረሻ እርሱን ላከው፡፡
\v 7 ገበሬዎቹ ግን እርስበርሳቸው እንዲህ አሉ፡፡ ይህ ወራሹ ነው ኑ እንግደለው ሀብቱ ሁሉ የእኛ ይሆናል ተባባሉ፡፡
\s5
\v 8 ልጁንም ያዙት፤ ገደሉት፤ከወይኑ ቦታ ውጭም ጣሉት፡፡
\v 9 የወይኑ ተክል ባለቤት በዚህ ጊዜ ምን ያደርጋል? ይመጣና ገበሬዎቹን ያጠፋቸዋል፤የወይን ቦታውንም ለሌሎች ይሰጣቸዋል፡፡
\s5
\v 10 ይህን የመጽሓፍ ቃል አላነበባችሁምን? እነሆ ግንበኞች የናቁት ድንጋይ እርሱ የማእዘን ድንጋይ ሆነ፤
\v 11 ይህ ከጌታ ነው፤ ለዐይኖቻችንም ድንቅ ነው፡፡
\v 12 ኢየሱስ ምሳሌውን የተናገረው ስለ እነርሱ እንደ ሆነ ስለ ተገነዘቡ እጃቸውን ሊጭኑበት ፈለጉ፤ነገር ግን ሕዝቡን ስለ ፈሩ፤ትተውት ሄዱ፡፡
\s5
\v 13 እነርሱም በንግግር እንዲያጠምዱት አንዳንድ ፈሪሳውያንና ከሄሮድስ ወገን የሆኑ ሰዎችን ላኩ፡፡
\v 14 ወደ እርሱ በመጡ ጊዜ እንዲህ አሉት፤መምህር ሆይ፣ አንተ እውነተኛ እንደ ሆንህ ለማንም በይሉኝታ እንደማታደርግ፣ለሰው ፊትም እንደማታዳላ ነገር ግን የእግዚአብሔርን መንገድ በእውነት እንደምታስተምር እናውቃለን፡፡ ለቄሳር ግብር መክፈል ተገቢ ነው? ወይስ አይደለም?
\v 15 እንክፈል ወይስ አንክፈል? አሉት፡፡ ኢየሱስ ግን ግብዝነታቸውን ዐውቆ ለምን ትፈትኑኛላችሁ? አላቸው፡፡ እንዳየው አንደ ዲናር አምጡልኝ አላቸው፡፡
\s5
\v 16 እነርሱም አመጡለት፡፡ ኢየሱስም ይህ ምስል ቅርጹም የማን ነው? አላቸው፡፡ እነርሱም የቄሳር ነው አሉት፡፡
\v 17 ኢየሱስም እንግዲህ የቄሳርን ለቄሳር የእግዚአብሔርንም ለእግዚአብሔር ስጡ አላቸው፡፡ እጅግም ተገረሙበት፡
\s5
\v 18 ትንሣኤ ሙታን የለም የሚሉ ሰዱቃውያን ወደ እርሱ መጥተው እንዲህ ብለው ጠየቁት፡፡
\v 19 መምህር ሆይ፣ ሙሴ፣ አንድ ሰው ልጅ ሳይወልድ ሚስቱን ትቶ ቢሞት፣ ወንድሙ እርስዋን አግብቶ ለወንድሙ ዘር ይተካለት ብሎ ጽፎልናል፡፡
\s5
\v 20 ሰባት ወንድማማቾች ነበሩ፡፡ የመጀመሪያው ሚስት አገባ፤ ዘር ሳይተካም ሞተ፡፡
\v 21 ሁለተኛውም አገባት፤ እርሱም ዘር ሳይተካለት ሞተ፡፡ ሦስተኛውም እንዲሁ፡፡
\v 22 ሰባቱም ለወንድማቸው ዘር አልተኩም፡፡ ከሁሉም በኋላ ሴቲቱም ደግሞ ሞተች፡፡
\v 23 ታዲያ ይህች ሴት በትንሣኤ የየትኛው ሚስት ትሆናለች? አሉት፡፡ ሰባቱም አግብተዋት ነበርና፡፡
\s5
\v 24 ኢየሱስም የምትስቱት መጻሕፍትንና የእግዚአብሔርን ኀይል ስለማታውቁ አይደለምን?
\v 25 በትንሳኤ ጊዜ ሰዎች አያገቡም፤ አይጋቡም፤ ነገር ግን በሰማይ እንደ መላእክት ይሆናሉ እንጂ፡፡
\s5
\v 26 ነገር ግን ሙታን እንደሚነሡ በሚነድደው ቁጥቋጦ ውስጥ እኔ የአብርሃም፣ የይስሐቅ፣ የያእቆብ አምላክ ነኝ ሲል እግዚአብሔር ለሙሴ የተናገረውን አላነበባችሁምን? እጅግ ትስታላችሁ፡፡
\v 27 እርሱ የሕያዋን አምላክ እንጂ የሙታን አምላክ አይደለም፡፡
\s5
\v 28 ከጸሓፍት አንዱ መጣና በአንድነት ሆነው ሲጠይቁት እንዴት በጥሩ ሁኔታ እንደ መላሰላቸው አይቶ፣ ከሕግ ፊተኛው የትኛው ነው? ብሎ ኢየሱስን ጠየቀው፡፡
\v 29 ኢየሱስም ፊተኛው፣ እስራኤል ሆይ ስማ! አምላካችን እግዚአብሔር አንድ እግዚአብሔር ነው፤
\v 30 አንተም አምላክህን እግዚአብሔርን በፍጹም ልብህ በፍጹም ነፍስህ፣በፍጹም አሳብህ፣ በፍጹምም ኀይልህ ውደድ የምትለዋ ናት፡፡
\v 31 ሁለተኛዋም ባልንጀራህን እንደ ራስህ ውደድ የምትለዋ ናት፡፡ ከእነዚህ የሚበልጥ ምንም ሌላ ትእዛዝ የለም አለው፡፡
\s5
\v 32 ሰውዬውም መምህር ሆይ፣በእውነት መልካም ብለሃል፤ እርሱ አንድ ነው፤ከእርሱም በቀር ሌላ የለም፤ እርሱን በፍጹም ልብ፣ በፍጹም ማስተዋል፣
\v 33 በፍጹም ኀይል መውደድና ባልንጀራን እንደ ራስ መውደድ ሁሉንም ዓይነት መስዋእትና የሚቃጠል መሥዋእት ከማቅረብ ይበልጣል አለ፡፡
\v 34 ኢየሱስም ሰውዬው በማስተዋል እንደ መለሰለት ባየ ጊዜ አንተ ከእግዚአብሔር መንግስት የራቅህ አይደለህም አለው፡፡ ከዚያ በኋላ ማንም ሰው ምንም ጥያቄ ሊጠይቀው አልደፈረም፡፡
\s5
\v 35 ኢየሱስም መለሰላቸው፤ በቤተ መቅደስ ውስጥ ሲያስተምር፣ ጸሓፍት ክርስቶስ የዳዊት ልጅ ነው የሚሉት እንዴት ነው? አለ፡፡
\v 36 ዳዊት ራሱ በመንፈስ ቅዱስ ጌታ ጌታዬን ጠላቶችህን የእግርህ መረገጫ እስካደርግልህ ድረስ በቀኜ ተቀመጥ አለው፡፡
\v 37 ዳዊት ራሱ ጌታዬ ብሎ ይጠራዋል፤ ታዲያ እንዴት ልጁ ይሆናል? ሕዝቡም በደስታ ይሰማው ነበር፡፡
\s5
\v 38 ኢየሱስም እንዲህ አለ፡፡ ከጸሓፍት ተጠንቀቁ፤ የተንዘረፈፈ ልብስ ለብሰው መሄድን ይወድዳሉ፤ እነርሱ በገበያ ቦታ ሰላምታን፣
\v 39 በምኩራብም የክብር ወንበር፣ በግብዣም የክብር ቦታ ላይ መቀመጥ ይወድዳሉ፡፡
\v 40 ለይምሰል ጸሎት በማስረዘም የመበለቶችን ቤት ይበዘብዛሉ፡፡ እነዚህ የባሰ ፍርድ ይቀበላሉ፡፡
\s5
\v 41 ኢየሱስም በመባ መቀበያው ፊት ለፊት ተቀመጠ፡፡ ብዙ ሰዎች በመባ መቀበያው ውስጥ ገንዘብ ሲጨምሩ ተመለከተ፡፡ ብዙ ሃብታሞች ብዙ ገንዘብ ይጨምሩ ነበር፡፡
\v 42 ከዚያም አንዲት ድኻ መበለት መጥታ ሁለት ናስ ጨመረች፤ይህም የብር ሩብ ነው፡፡
\s5
\v 43 እርሱም ደቀመዛሙርቱን ወደ ራሱ ጠርቶ እንዲህ አላቸው፡፡ እውነት እውነት እላችኋለሁ፤ይህች መበለት በመባ መቀበያው ውስጥ ገንዘባቸውን ከጨመሩት ሁሉ አብልጣ ሰጠች፡፡
\v 44 እነርሱ ከትርፋቸው ሰጥተዋልና፡፡ እርስዋ ግን ከጉድለቷ ሰጠች፤ ያላትን ሁሉ ሰጠች፤ ኑሮዋን እንኳ ሳይቀር ሁሉንም ሰጠች፡፡
\s5
\c 13
\cl ምዕራፍ 13
\p
\v 1 ኢየሱስ ከቤተመቅደስ ሲወጣ ሳለ ከደቀመዛሙርቱ አንዱ መምህር ሆይ፤ እንዴት ያሉ ድንጋዮችና እንዴት ያሉ ሕንጻዎቹ እንደሆኑ ተመልከት! አለው፡፡
\v 2 እርሱም እነዚህን ታላላቅ ሕንጻዎች ታያለህን? ድንጋይ በድንጋይ ላይ ሳይፈርስ እንደዚህ አይቀርም አለው፡፡
\s5
\v 3 ኢየሱስ በደብረዘይት ተራራ ላይ በቤተመቅደሱ ትይዩ ተቀምጦ ሳለ ጴጥሮስ፣ ያዕቆብ፣ ዮሐንስና እንድርያስ
\v 4 ንገረን፣ እነዚህ ነገሮች የሚሆኑት መቼ ነው? እነዚህ ነገሮች ሁሉ የሚፈጸሙበት ምልክቱስ ምንድነው? ብለው ለብቻው ጠየቁት፤
\s5
\v 5 ኢየሱስም ማንም እንዳያስታችሁ ለራሳችሁ ተጠንቀቁ አላቸው፡፡
\v 6 ብዙዎች እኔ ክርስቶስ ነኝ! እያሉ በስሜ ይመጣሉና ብዙዎችንም ያስታሉ፡፡
\s5
\v 7 ጦርነትንና የጦርነትን ወሬ በምትሰሙበት ጊዜ አትታወኩ፤ እነዚህ ነገሮች የግድ መፈጸም አለባቸው፤ ነገር ግን መጨረሻው ገና ነው፡፡
\v 8 ሕዝብ በሕዝብ ላይ፣ መንግሥትም በመንግሥት ላይ ይነሣልና፡፡ በተለያዩ ቦታዎች የምድር መንቀጥቀጥ፣ ረሃብም ይሆናል፡፡ እነዚህ የምጥ ጣር መጀመሪያ ናቸው፡፡
\s5
\v 9 እናንተ ግን ለራሳችሁ ተጠንቀቁ፡፡ ወደ ሸንጎዎቻቸው ያቀርቧችኋል፣ በምኩራቦች ውስጥ ትደበደባላችሁ፡፡ ለእነርሱ ምስክር እንዲሆን በእኔ ምክንያት በገዢዎችና በነገሥታት ፊት ትቆማላችሁ፡፡
\v 10 አስቀድሞ ወንጌል ለሕዝቦች ሁሉ ይሰበካል፡፡
\s5
\v 11 ወደ ፍርድ በሚያቀርቧችሁና አሳልፈው በሚሰጧችሁ ጊዜ አስቀድማችሁ ምን እንደምትናገሩ አትጨነቁ፤ ነገር ግን በዚያች ሰዓት የምትናገሩት ይሰጣችኋልና፤ የሚናገረውም መንፈስ ቅዱስ ነው እንጂ እናንተ አይደላችሁም፡፡
\v 12 ወንድም ወንድሙን ለሞት አሳልፎ ይሰጣል፣ አባትም ልጁን፤ ልጆችም ወላጆቻቸውን በመቃወም ተነስተው ይገድሏቸዋል፡፡
\v 13 ስለስሜም በሰዎች ሁሉ ትጠላላችሁ፡፡ ነገር ግን እስከ መጨረሻው የሚጸና እርሱ ይድናል፡፡
\s5
\v 14 የጥፋትን እርኩሰት በማይገባው ቦታ ቆሙ ስታዩት (አንባቢው ያስተውል) በይሁዳ ያሉ ወደ ተራሮች ይሽሹ፤
\v 15 በቤቱ ጣሪያ ላይ ያለም አንዳች ይወስድ ዘንድ አይውረድ፣ ወደ ቤትም አይግባ፤
\v 16 በእርሻም ያለ ልብሱን ይወስድ ዘንድ ወደ ኋላው አይመልከት፡፡
\s5
\v 17 ነገር ግን በእነዚያ ወራት ለእርጉዞችና ለሚያጠቡ ወዮላቸው!
\v 18 በክረምት እንዳይሆን ጸልዩ፡፡
\v 19 እግዚአብሔር ከፈጠረው ከፍጥረት መጀመሪያ ጀምሮ እስካሁን ድረስ ያልሆነ ወደፊትም የማይሆን ታላቅ መከራ በእነዚያ ቀናት ይሆናልና፡፡
\v 20 ጌታ ቀኖቹን ባያሳጥር ኖሮ ሥጋን የለበሰ ሁሉ አይድንም ነበር፡፡ ነገር ግን ስለመረጣቸው ስለ ምርጦቹ ሲል ቀኖቹን አሳጠረ፡፡
\s5
\v 21 አንድ ሰው እነሆ ክርስቶስ በዚህ ነው ወይም እነሆ በዚያ ነው ቢላችሁ አትመኑት፡፡
\v 22 ሐሰተኛ ክርስቶሶችና ሐሰተኛ ነብያት ይነሣሉና፤ ቢቻላቸው የተመረጡትን ለማሳት ድንቆችንና ምልክቶችን ያሳያሉ፡፡
\v 23 ነገር ግን አስተውሉ፤ እነሆ አስቀድሜ ሁሉንም ነገር ነግሬአችኋለሁ፡፡
\s5
\v 24 ከመከራው በኋላ በእነዚያ ቀናት ፀሐይ ትጨልማለች፣ ጨረቃም ብርሃንዋን አትሰጥም፣
\v 25 ከዋክብትም ከሰማይ ይወድቃሉ፣ በሰማያት ውስጥ ያሉ ኃይላትም ይናወጣሉ፡፡
\v 26 እነርሱም የሰው ልጅ በደመና ውስጥ በታላቅ ኃይልና ክብር ሲመጣ ያዩታል፡፡
\v 27 ከምድር ጫፍ እስከ ጫፍ ለእርሱ የተመረጡትን ከአራቱም ነፋሳት በአንድ ላይ እንዲሰበስቡለት መላዕክትን ይልካቸዋል፡፡
\s5
\v 28 ምሳሌውን ከበለስ ዛፍ ተማሩ፤ ቅርንጫፏ ሲለሰልስ፣ ቅጠሏም ሲያቆጠቁጥ ያን ጊዜ በጋ መቃረቡን ታውቃላችሁ፡፡
\v 29 እናንተም ደግሞ እነዚህ ነገሮች ሲፈጸሙ በምታዩበት ጊዜ የሰው ልጅ በበር ላይ መሆኑን ታውቃላችሁ፡፡
\s5
\v 30 እውነት እላችኋለሁ፣ እነዚህ ነገሮች እስኪፈጸሙ ድረስ ይህ ትውልድ አያልፍም፡፡
\v 31 ሰማይና ምድር ያልፋል፣ ቃሌ ግን አያልፍም፡፡
\v 32 ስለዚያች ቀን ወይም ስለዚያች ሰዓት ግን ከአባት በስተቀር የሰማይ መላዕክትም ቢሆኑ፣ ልጅም ቢሆን ማንም አያውቅም፡፡
\s5
\v 33 ጊዜው መቼ እንደሆነ አታውቁምና አስተውሉ፣ ንቁና ጸልዩ፡፡
\v 34 ነገሩ ለአገልጋዮቹ ሥልጣን፣ ለእያንዳንዳቸውም የሥራ ድርሻ በመስጠት ዘበኛውም ደግሞ እንዲጠብቅ አዝዞት ቤቱን ትቶ ወደ ሩቅ ሀገር የሚሔድን ሰው ይመስላል፡፡
\s5
\v 35 35የቤቱ ጌታ በምሽት፣ ወይም በእኩለ ሌሊት፣ ወይም ዶሮ ሲጮህ፣ ወይም ጠዋት ላይ ምን ጊዜ እንደሚመጣ አታውቁምና እንግዲህ ንቁ!
\v 36 በድንገት ሲመጣ እንቅልፍ ላይ ሆናችሁ እንዳያገኛችሁ፡፡
\v 37 ለእናንተ የምነግራችሁን ለሁሉም እናገራለሁ፣ንቁ!
\s5
\c 14
\cl ምዕራፍ 14
\p
\v 1 ከሁለት ቀን በኋላ የፋሲካና የቂጣ በዓል ነበር፡፡ የካህናት አለቆችና ጸሓፍት እንዴት አድርገው በተንኮል ይዘው ሊገድሉት እንደሚችሉ ያስቡ ነበር፡፡
\v 2 ነገር ግን የህዝብ ሁከት እንዳይሆን በበዓል ቀን አይሁን ተባብለው ነበር፡፡
\s5
\v 3 እርሱም በቢታኒያ በለምጻሙ በስምዖን ቤት በማዕድ ተቀምጦ ሳለ አንዲት ሴት ዋጋው እጅግ የከበረ ሽቱ የያዘ የአልባስጥሮስ ጠርሙስ ይዛ መጣች፡፡ ጠርሙሱንም ሰብራ ሽቱውን በኢየሱስ በራሱ ላይ አፈሰሰች ፡፡
\v 4 ነገር ግን ከመካከላቸው አንዳንዶቹ እንዲህ ያለው የሽቱ ማባከን ያስፈለገው ለምንድነው በማለት የተበሳጩ አንዳንድ ሰዎች ነበሩ
\v 5 ይህ ቅባት ከሦስተ መቶ ሽልንግ በላይ ተሸጦ ለድሆች ሊሰጥ ይቻል ነበር እያሉ በእርሷ ላይ አጉረመረሙ፡፡
\s5
\v 6 ኢየሱስ ግን ተዋት ለምን ታስቸግሯታላችሁ እርሷ መልካምን ነገር አድርጋልኛለች፡፡
\v 7 ድሆች ሁሉጊዜ ከእናንተ ጋር ናቸው በፈለጋችሁም ጊዜ መልካም ልታድጉላቸው ትችላላችሁ እኔን ግን ሁልጊዜ አታገኙኝም፡፡
\v 8 እርሷ ከመቃብር በፊት ሰውነቴን ሽቱ በመቀባት የምትችለውን አድርጋለች፡፡
\v 9 ደግሞም እውነት እላችኋለሁ ይህ ወንጌል በዓለም ዙሪያ በሚሰበክበት ጊዜ ሁሉ ይህች ሴት ያደረገችው ነገር ለመታሰቢያዋ ይነገራል አላቸው፡፡
\s5
\v 10 ከአስራ ሁለቱ አንዱ የሆነው የአስቆሮቱ ይሁዳ እንዴት አሳልፎ ይሰጠው ዘንድ ወደ ካህናት አለቆች ሄደ
\v 11 እነርሱም በሰሙ ጊዜ ደስ አላቸው ገንዘብም ሊሰጡት ቃል ገቡለት፡፡እርሱም አሳልፎ ሊሰጠው አመቺ ጊዜ ይጠብቅ ነበር፡፡
\s5
\v 12 የፋሲካን መስዋዕት በሚያቀርቡበት በቂጣ በዓል የመጀመሪው ቀን ደቀመዛሙርቱ ፋሲካን ትበላ ዘንድ የት እናዛገጅልህ ብለው ጠየቁት፡፡
\v 13 እርሱም ከደቀመዛሙርቱ ሁለቱን ልኮ ወደ ከተማ ሂዱ ወዲያውም አንድ ሰው ውሃ ተሸክሞ ታገኛላችሁ ተከትላችሁትም ሂዱና
\v 14 ወደሚገባበት ቤት ገብታችሁ የቤቱን ባለቤት መምህሩ ከደቀመዛሙርቴ ጋር ፋሲካን እበላ ዘንድ የእንግዳ ክፍሌ የትኛው ነው ብሎሀል ብላችሁ ጠይቁት
\s5
\v 15 እርሱ ራሱ በሰገነት ላይ ያለ በቤት ዕቃ የተደራጀና የተዘጋጀ ሰፊ አዳራሽ ያሳያችኋል በዚያም አዘጋጁልን ፡፡
\v 16 ደቀመዛሙርቱም ወጥተው ወደ ከተማ መጡ ልክ እንዳላቸውም አገኙ ፋሲካንም አዘጋጁ፡፡
\s5
\v 17 በመሸም ጊዜ ከአስራ ሁለቱ ጋር መጣ፡፡
\v 18 ተቀምጠውም በመመገብ ላይ ኢየሱስ አውነት እላችኋለሁ በማዕድ ከኔ ጋር ያለ ከእናንተ አንዱ አሳልፎ ይሰጠኛል አላቸው፡፡
\v 19 እነርሱም እጅግ አዝነው በየተራ እኔ እሆንን ይሉት ጀምር፡፡
\s5
\v 20 ኢየሱስም ከእኔ ጋር ወደ ወጥ ሳህኑ የሚነክረውና ከአስራሁለቱ አንዱ ነው አላቸው፡፡
\v 21 የሰው ልጅስ ስለ እርሱ እንደተጻፈው ይሄዳል የሰው ልጅ አሳልፎ ለሚሰጠው ለዚያ ሰው ግን ወዮለት ባይወለድ ይሻለው ነበር አላቸው፡፡
\s5
\v 22 እየተመገቡም ሳለ እንጀራን አንስቶ ከባረከ በኋላ ቆርሶ ሰጣቸውና ውሰዱና ብሉ ይህ ስጋዬ ነው አላቸው፡፡
\v 23 እንዲሁም ጽዋውን አንስቶ አመስግኖ ለደቀመዛሙርቱ ሰጣቸው ሁሉም ጠጡ፡፡
\v 24 እርሱም ይህ ለብዙዎች የሚፈስ የቃል ኪዳን ደሜ ነው ፡፡
\v 25 እውነት እላችኋለሁ በእግዚአብሔር መንግስት እንደገና እንደ አዲስ እስከምጠጣበት ቀን ድረስ ከዚህ ወይን ከዚህ በኋላ አልጠጣም፡፡
\s5
\v 26 መዝሙርም ከዘመሩም በኋላ ወደ ደብረ ዘይት ተራራ ሄዱ፡፡
\v 27 ኢየሱስም እረኛውን እመታለው በጎቹም ይበታተናሉ ተብሎ እንደተጻፈ ሁላችሁ ትሰናከላላችሁ
\s5
\v 28 ከተነሳሁ በኋላ ግን ወደ ገሊላ እቀድማችኋለሁ አላቸው፡፡
\v 29 ጴጥሮስም ሁሉ ቢሰናከሉ እኔ ግን አልሰናከልም አለው፡፡
\s5
\v 30 ኢየሱስም አውነት እልሃለሁ ዛሬ ሌሊት ዶሮ ሁለት ጊዜ ሳይጮህ ሶስት ጊዜ ትክደኛለህ አለው፡፡
\v 31 እርሱ ግን እጅግ እየጮኸ እስከሞት እንኳ ቢሆን አልክድህም አለው፡፡ ሌሎቹም እንደዚያው አሉ፡፡
\s5
\v 32 ጌቴ ሴማኒ ወደሚባል ሥፍራም መጡ፡፡ ደቀመዛሙርቱንም እስክ ጸልይ ድረስ በዚህ ተቀመጡ አላቸው፡፡
\v 33 ኢየሱስም ጴጥሮስን ያዕቆብንና ዮሐንስን ይዞ ሄደ እጅግ ሊያዝንና ሊተክዝ ጀመረ፡፡
\v 34 ነፍሴ እስከሞት ድረስ እጅግ አዝናለች በዚህ ሆናችሁ ትጉ ንቁም አላቸው፡፡
\s5
\v 35 ጥቂትም ፈቀቅ ብሎ ሄደ፤ በግንባሩም ተደፍቶ የሚቻል ከሆነ ይህች ሰዓት ሰዓቲቱ እንድታልፍ መጸለይ ጀመረ፡፡
\v 36 አባት ሆይ ለአንተ ሁሉ ይቻላል ይህች ጽዋ ከእኔ ትለፍ ነገር ግን የእኔ ሳይሆን የአንተ ፈቃድ ይሁን አለ፡፡
\s5
\v 37 ወደ እነርሱም መጣ ተኝተውም አገኛቸው ጴጥሮስንም ስምዖን ተኝተሀልን ለአንድ ሰዓት እንኳ ልትተጋ አልቻልክምን፡፡
\v 38 ወደ ፈተና እንዳትገቡ ትጉና ጸልዩ፡፡ መንፈስ ዝግጁ ነው ሥጋ ግን ደካማ ነው አለው፡፡
\v 39 ተመልሶም ሄደና ያንኑ ቃል ደግሞ ጸለየ፡፡
\s5
\v 40 እንደገና ወደ ደቀመዛሙርቱ በመጣ ጊዜ አሁንም ተኝው አገኛቸው አይናቸው በእንቀልፍ ከብዶ ስለነበር የሚመልሱለትንም አያውቁም ነበር፡፡
\v 41 ለሦስተኛም ጊዜ ወደ እነርሱ መጣና እንግዲህስ ይበቃል ተኙ እረፉም የሰው ልጅ ለኃጢአተኞች አልፎ ይሰጥ ዘንድ ሰዓቲቱ ደርሳለች ፡፡
\v 42 ተነሱ እንሂድ እነሆ አሳልፎ የሚሰጠኝ በደጅ ነው አላቸው፡፡
\s5
\v 43 ወዲያውም ገና በመናገር ላይ ሳለ ከአስራ ሁለቱ አንዱ የነበረው የአስቆሮቱ ይሁዳ መጣ ፡፡ ከእርሱም ጋር ከካህናት አለቆች፣ ከጸሓፍትና ከሽማግሌዎች ዘንድ የተላኩ ብዙ ህዝብ ሠይፍና ቆመጥ ይዘው መጡ፡፡
\v 44 አሳልፎ የሚሰጠውም የምስመው እርሱ ነውና ያዙት በጥንቃቄ ውሰዱት ብሎ ምልክት ሰጥቷቸው ነበር፡፡
\v 45 በመጣም ጊዜ በቀጥታ ወደ ኢየሱስ ቀርቦ መምህር ሆይ ብሎ ሳመው፡፡
\v 46 እነርሱም ይዘው ወሰዱት፡፡
\s5
\v 47 ነገር ግን በዚያ ከቆሙት መካከል አንዱ ሰይፉን መዘዘ፤ የሊቀ ካህናቱን አገልጋይ ጆሮም ቆረጠው፡፡
\v 48 ኢየሱስም መልሶ ወንበዴ እንደምትይዙ ሰይፍና ቆመጥ ይዛችሁ ልትይዙኝ መጣችሁን
\v 49 በየዕለቱ በቤተ መቅደስ እያስተማርከ ከእናንተ ጋር በነበርኩ ጊዘ አልያዛችሁኝም፡፡ ነገር ግን የተጻፈው ይፈጸም ዘንድ ይህ ሆኗል አላቸው፡፡
\v 50 ሁሉም ትተውት ሸሹ፡፡
\s5
\v 51 እርቃኑን ከበፍታ በተሰራ ጨርቅ የሸፈነ አንድ ወጣት ይከተለው ነበር ሊይዙትም ባሉ ጊዜ
\v 52 የበፍታ ጨርቁን ነጠላውን ትቶ ራቁቱን አመለጠ፡፡
\s5
\v 53 ኢየሱስንም ወደ ሊቀ ካህናቱ ይዘውት መጡ፡፡ የካህናት አለቆች፣ ሽማግሌዎችና ጸሓፍትም አብረውት መጡ፡፡
\v 54 ጴጥሮስም እስከ ሊቀካህናቱ ግቢ ድረስ በሩቅ ሆኖ ይከተለው ነበር፡፡ ከዚያም ከጠበቃዊዎች ጋር እሳት እየሞቀ ተቀመጠ፡፡
\s5
\v 55 ሊቀ ካህናቱና ጉባኤው ሁሉ በኢየሱስ ላይ ሞት የሚያስፈርድበት ምክንያት ይፈልጉ ነበር ነገር ግን ሊያገኙ አልቻሉም፡፡
\v 56 ብዙዎች በሀሰት ቢመሰክሩበትም ምስክርነታቸው እርስ በእርሱ የሚጣረስ ነበር፡፡
\s5
\v 57 ሦስት ሰዎችም ተነስተው በሀሰት መሰከሩበት እንዲህም አሉ
\v 58 ይህንን በእጅ የተሰራ ቤተመቅደስ በሶስት ቀን አፍርሼ እንደገና በሶስት ቀን ውስጥ በእጅ ያልተሰራ ሌላ ቤተመቅደስ እሰራለሁ ሲል ሰምተነዋል ፡፡
\v 59 የእነርሱም ምስክርነት ቢሆን እርስ በእርሱ የሚጣረስ ነበረ፡፡
\s5
\v 60 ሊቀ ካህናቱም ተነስቶ በመካከል ቆመና ለሚመሰክሩብህ መልስ አትሰጥምን ብሎ ጠየቀው፡፡
\v 61 ኢየሱስ ግን ዝም አለ መልስም አልሰጠም፡፡ ሊቀ ካህናቱም በድጋሚ የቡሩኩ ልጅ መሲሁ አንተ ነህን ብሎ ጠየቀው
\v 62 ኢየሱሰም አዎ ነኝ የሰው ልጅ በኃይሉ ቀኝ ተቀምጦ በሰማይ ደመና ሲመጣ ታዩታላችሁ አለው፡፡
\s5
\v 63 ሊቀካህናቱም ልብሱን ቀደደና ከእንግዲህ ምን ሌላ ምስክር ያስፈልጋል
\v 64 እግዚአብሔርን ሲሳደብ ሰምታችኋል ታዲያ ምን ታስባለችሁ ፡፡ ሁሉም ሞት ይገባዋል አሉ፡፡
\v 65 አንዳነዶቹም ይተፉበት ፊቱንም ሸፍነው ትንቢት ተናገር እያሉ ያሾፉበት ጀመር፡፡ መኮንኖችም በእጃቸው እየጎሰሙ ወሰዱት፡፡
\s5
\v 66 ጴጥሮስም በሊቀ ካህናቱ ግቢ እሳት በመሞቅ ላይ ሳለ
\v 67 አንዲት የሊቀ ክህናቱ የቤት ውስጥ ሠራተኛ አየችውና አንተ በትክክል ከናዝሬቱ ኢየሱስ ጋር ነበርክ አለችው፡፡
\v 68 እርሱ ግን የምትይውን አላውቀውም ምን እንደምታወሪም አልገባኝም ብሎ ካደ፡፡ ወደ ዋናው በር መግቢያ በሄደ ጊዜ ዶሮ ጮኸ
\s5
\v 69 ሠራተኛይቱም አይታው በዚያ ላሉት ወታደሮች ይህ ከእነርሱ አንዱ ነው አለቻቸው፡፡
\v 70 እርሱ ግን እንደገና ካደ፡፡ ከጥቂት ጊዜ በኋላ በዚያ ከቆሙት መካከል አንዳንዶቹ ጴጥሮስን አንተ የገሊላ ሰው ስለሆንክ በትክክል ከእነርሱ አንዱ ነህ አሉት፡፡
\s5
\v 71 እርሱም የምትሉትን ሰው አላውቀውም ብሎ መማልና መራገም ጀመረ፡፡
\v 72 ወዲያውም ለሁለተኛ ጊዜ ዶሮ ጮኸ ጴጥሮስም ኢየሱስ ዛሬ ሌሊት ዶሮ ሁለት ጊዜ ሳይጮህ ሶስት ጊዜ ትክደኛለህ ያለውን ቃል አስታወሰ ነገሩንም ባሰበ ጊዜ አለቀሰ፡፡
\s5
\c 15
\cl ምዕራፍ 15
\p
\v 1 ወዲያውኑም በማለዳ የካህናት አለቆች ከሽማግሌዎች፣ ከጸሓፍት፣ ከሸንጎም አባሎችም ሁሉ ጋር ተማከሩ፤ ኢየሱስን አስረው ወሰዱትና ለጲላጦስ አሳልፈው ሰጡት።
\v 2 ጲላጦስም፣አንተ የአይሁድ ንጉሥ ነህን? ብሎ ጠየቀው። ኢየሱስም ሲመልስ አንተ እንዳልከው ነኝ አለው።
\v 3 የካህናት አለቆችም ብዙ ክስ አቀረቡበት።
\s5
\v 4 ጲላጦስም ስንት ክስ እንዳቀረቡብህ ተመልከት! ምንም አትመልስምን? ብሎ እንደገና ጠየቀው።
\v 5 ኢየሱስ ግን ጲላጦስ እስኪደነቅ ድረስ ምንም መልስ አልሰጠም።
\s5
\v 6 በየበዓሉ ሕዝቡ ጲላጦስ እንዲፈታላቸው የጠየቁትን አንድ እስረኛ የመፍታት ልማድ ነበረው።
\v 7 በዚያም ኹከት ቀስቅሰው ግድያ ከፈጸሙ ሰዎች ጋር የታሰረ አንድ በርባን የሚባል ሰው ነበር።
\v 8 ሕዝቡም ወደ ጲላጦስ ቀርበው የተለመደውን እንዲያደርግላቸው ጠየቁት።
\s5
\v 9 ጲላጦስም "የአይሁድን ንጉሥ" እንድፈታላችሁ ትፈልጋላቸሁን? አላቸው።
\v 10 እንዲህ ያለው የካህናት አለቆች ኢየሱስን አሳልፈው የሰጡት በቅናት መሆኑን ያውቅ ስለ ነበር ነው።
\v 11 የካህናት አለቆች ግን በእርሱ ፈንታ በርባን እንዲፈታላቸው ጲላጦስን እንዲጠይቁ ሕዝቡን ቀሰቀሱ።
\s5
\v 12 ጲላጦስም መልሶ ታዲያ በዚህ የአይሁድ ንጉሥ ብላችሁ በምትጠሩት ሰው ላይ ምን ላድርግበት? አላቸው።
\v 13 እነርሱም "ስቀለው!" እያሉ እንደገና ጮኹ።
\s5
\v 14 ጲላጦስም "ለምን? ምን በደል ፈጽሟል?" አላቸው። እነርሱም "ስቀለው!" እያሉ አብዝተው ጮኹ።
\v 15 ጲላጦስም ሰዎቹን ደስ ለማሰኘት ብሎ በርባንን ፈቶ ለቀቀላቸው፤ኢየሱስን ግን አስገርፎ እንዲሰቀል አሳልፎ ሰጠው።
\s5
\v 16 ወታደሮቹም ኢየሱስን ፕራይቶሪዮን ወደሚባለው ግቢ ወሰዱት፤ወታደሮቹንም ሁሉ ጠሩ፤
\v 17 ሐምራዊ ልብስ አለበሱት፤ የእሾኽ አክሊልም በራሱ ላይ ደፉበት፡፡
\v 18 "የአይሁድ ንጉሥ ሆይ! ሰላም ለአንተ ይሁን!" እያሉ ሰላምታ ይሰጡት ነበር።
\s5
\v 19 በመቃ ዐናቱን እየመቱ፤ ምራቃቸውን ተፉበት፤ በፊቱም ተንበርክከው ሰገዱለት።
\v 20 አላግጠውበትም ሐምራዊውን ልብስ አወለቁበት፤ የራሱንም ልብስ አልብሰው፤ሊሰቅሉ ወሰዱት።
\v 21 በመንገድ ሳሉም የቀሬና ሰው የሆነውን የእስክንድርንና የሩፎስን አባት ስምዖንን ከገጠር ሲመጣ አግኝተው፤ የኢየሱስን መስቀል ተሸክሞ ከእነርሱ ጋር እንዲሄድ አስገደዱት።
\s5
\v 22 ከዚያም በኋላ ኢየሱስን ጎልጎታ ተብሎ ወደሚጠራው ቦታ ወሰዱት፤ ትርጉሙም፡- "የራስ ቅል ስፍራ" ማለት ነው።
\v 23 ከከርቤ ጋር የተቀላቀለ የወይን ጠጅም ሰጡት፤ እርሱ ግን አልጠጣውም።
\v 24 ከዚያም ሰቀሉት፤ ልብሶቹንም ማን ምን እንደሚወስድ ዕጣ ተጣጥለው ተከፋፈሉ።
\s5
\v 25 ከጧቱ ሦስት ሰዓት ሲሆን ሰቀሉት፡፡
\v 26 "የአይሁድ ንጉሥ" የሚል የክስ ጽሑፍ በመስቀሉ ዐናት ተጽፎ ነበር።
\v 27 ከኢየሱስም ጋር ሁለት ወንበዴዎችን አንዱን በቀኙ፣አንዱንም በግራው ሰቀሉ።
\v 28 መጽሓፍ "ከዐመፀኞች ጋር ተቈጠረ፤" የሚለው ቃል ተፈጸመ።
\s5
\v 29 በአጠገቡ ያልፉ የነበሩትም ሰዎች ራሳቸውን በንቀት እየነቀነቁ እንዲህ በማለት ይሰድቡት ነበር፣ "አንተ ቤተ መቅደስን አፍርሰህ በሦስት ቀን የምትሠራ ሆይ!
\v 30 እስቲ አሁን ራስህን አድን፤ከመስቀልም ውረድ!"
\s5
\v 31 እንደዚሁም የካህናት አለቆች ከጸሓፍት ጋር ሆነው እርስበርሳቸው እንዲህ እያሉ ያፌዙበት ነበር፤ "ሌሎችን አድኖአል፤ ራሱን ማዳን ግን አይችልም" አሉ፡፡
\v 32 "አይተን እንድናምንበት መሲሑ የእስራኤል ንጉሥ እስቲ አሁን ከመስቀል ይውረድ" ከእርሱ ጋር የተሰቀሉት ወንበዴዎችም ይሰድቡት ነበር።
\s5
\v 33 ከቀኑም ስድስት ሰዓት ጀምሮ እስከ ዘጠኝ ሰዓት ድረስ በምድሪቱ ሁሉ ላይ ጨለማ ሆነ።
\v 34 ዘጠኝ ሰዓት ሲሆን ኢየሱስ፣ "ኤሎሄ፣ ኤሎሄ፣ ላማሰበቅታኒ፤" ብሎ በታላቅ ድምፅ ጮኸ። ትርጓሜውም "አምላኬ፣ አምላኬ ለምን ተውከኝ?" ማለት ነው።
\v 35 በዚያም ቆመው ከነበሩት ሰዎች አንዳንዶቹ ሰምተው "እነሆ! ኤልያስን ይጣራል፤" አሉ።
\s5
\v 36 ከእነርሱም አንዱ ሮጠና ሆምጣጤ በሰፍነግ ሞላ፤ "ኤልያስ መጥቶ ያወርደው እንደ ሆነ እንይ" አለ።እንዲጠጣውም በመቃ ላይ አድርጎ ለኢየሱስ ሰጠው፡፡
\v 37 ከዚያም ኢየሱስ በታላቅ ድምፅ ጮኸ፤ መንፈሱንም ሰጠ።
\v 38 የቤተ መቅደሱም መጋረጃ ከላይ እስከ ታች ተቀዶ ከሁለት ተከፈለ።
\s5
\v 39 በመስቀሉ ፊት ለፊት ቆሞ የነበረ የመቶ አለቃ ኢየሱስ እንዴት መንፈሱን እንደ ሰጠ ባየ ጊዜ፣ "ይህ ሰው በእርግጥ የእግዚአብሔር ልጅ ነበር፤" አለ።
\v 40 በሩቅ ሆነው የሚመለከቱ ሴቶችም በዚያ ነበሩ። ከእነርሱም መካከል መግደላዊት ማርያም፣ የታናሹ ያዕቆብና የዮሳ እናት ማርያም፣ሰሎሜም ነበሩ።
\v 41 እነርሱ ኢየሱስ በገሊላ በነበረበት ጊዜ ይከተሉትና ያገለግሉት ነበር። እንዲሁም ከኢየሱስ ጋር ወደ ኢየሩሳሌም የመጡ ሌሎች ብዙ ሴቶችም ነበሩ።
\s5
\v 42 መሽቶ ስለ ነበርና የሰንበት ዋዜማና ለሰንበት የመዘጋጃ ጊዜ ስለ ነበር፡፡
\v 43 የተከበረ የሸንጎ አባል የነበረ ዮሴፍ የሚባል የአርማትያስ ሰው መጣ። እርሱም የእግዚአብሔርን መንግሥት የሚጠባበቅ ሰው ነበር። በድፍረትም ወደ ጲላጦስ ፊት ቀርቦ የኢየሱስን አስከሬን እንዲሰጠው ለመነው።
\v 44 ጲላጦስም "እንዴት እንዲህ በቶሎ ሞተ?" ብሎ ተደነቀ። የመቶ አለቃውንም ጠርቶ፣ "ከሞተ ቈይቶአልን?" ሲል ጠየቀው።
\s5
\v 45 የኢየሱስን መሞት ከመቶ አለቃው ከሰማ በኋላ አስከሬኑን እንዲወስድ ለዮሴፍ ፈቀደለት።
\v 46 ዮሴፍም የከፈን ልብስ ገዛ፤ የኢየሱስን አስከሬን ከመስቀል አውርዶ ገነዘው፤ ከዐለት ተወቅሮ በተዘጋጀ መቃብር ውስጥ አስቀመጠው። ትልቅ ድንጋይም አንከባሎ የመቃብሩን መግቢያ ዘጋ።
\v 47 መግደላዊት ማርያምና የዮሳ እናት ማርያምምሰ ኢየሱስን የት እንዳኖሩት አዩ።
\s5
\c 16
\cl ምዕራፍ 16
\p
\v 1 ሰንበት ካለፈ በኋላም መጥተው ይቀቡት ዘንድ መግደላዊት ማርያም፣ የያዕቆብ እናት ማርያምና ሰሎሜ ሽቶ ገዙ፡፡
\v 2 ከሳምንቱም በመጀመሪያው ቀን ጎህ በቀደደ ጊዜ ወደ መቃብሩ መጡ፡፡
\s5
\v 3 እርስ በርሳቸውም ድንጋዩን ከመቃብሩ መግቢያ ማን ያንከባልልናል ይባባሉ ነበር፡፡
\v 4 አሻግረው ሲመለከቱም ድንጋዩ እጅግ ትልቅ ነበርና ተንከባሎ አዩት፡፡
\s5
\v 5 ወደ መቃብሩም ገብተው የሚያንጸባርቅ ነጭ ልብስ የለበሰ አንድ ወጣት በስተቀኝ ተቀምጦ አዩና ተገረሙ፡፡
\v 6 እርሱም አትገረሙ፣ የምትፈልጉት ተሰቅሎ የነበረውን የናዝሬቱን ኢየሱስን ነው፡፡ ያኖሩበትን ቦታ ተመልከቱ፤ እርሱ በዚህ የለም፣ ተነሥቷል፡፡
\v 7 ነገር ግን ሂዱ፣ ለጴጥሮስና ለደቀመዛሙርቱም እንደነገራችሁ ወደ ገሊላ ይቀድማችኋል፣ በዚያም ታዩታላችሁ ብላችሁ ንገሯቸው አላቸው፡፡
\s5
\v 8 እነርሱም መገረምና ፍርሃት ወድቆባቸው ነበርና ከዚያ ወጥተው ከመቃብሩ ሸሹ፡፡ ፈርተውም ነበርና ለማንም አንዳች አልተናገሩም፡፡
\s5
\v 9 ከሳምንቱም በመጀመሪያው ቀን በማለዳ በተነሳ ጊዜ ሰባት አጋንንት አውጥቶላት ለነበረችው ለመግደላዊት ማርያም አስቀድሞ ታያት፡፡
\v 10 እርሷም ከኢየሱስ ጋር የነበሩት እያዘኑና እያለቀሱ ሳሉ ሄዳ ነገረቻቸው፡፡
\v 11 እነርሱም ሕያው እንደሆነና ለእርሷም እንደታያት በሰሙ ጊዜ አላመኑም፡፡
\s5
\v 12 ከእነዚህ ነገሮች በኋላም ከእነርሱ ሁለቱ ወደ ገጠር በመሄድ ላይ ሳሉ ኢየሱስ በሌላ ሰው መልክ ተገለጠላቸው፡፡
\v 13 እነርሱም ሄደው ለተቀሩት ነገሯቸው፤ እነርሱንም አላመኗቸውም፡፡
\s5
\v 14 ከዚያም በማዕድ ተቀምጠው ሳሉ ለአሥራ አንዱ ለራሳቸው ኢየሱስ ተገለጠላቸውና ስለ ልባቸው ጥንካሬና ከትንሳኤው በኋላ ያዩትን ስላላመኗቸው ወቀሳቸው፡፡
\v 15 እንዲህም አላቸው፣ ወደ ዓለም ሁሉ ሂዱ፣ ወንጌልንም ለፍጥረት በሙሉ ስበኩ አላቸው፡፡
\v 16 ያመነና የተጠመቀም ይድናል፣ ያላመነ ግን ይፈረድበታል፡፡
\s5
\v 17 ያመኑትንም እነዚህ ምልክቶች ይከተሏቸዋል፤ በስሜ አጋንንትን ያወጣሉ፣ በአዲስ ቋንቋ ይናገራሉ፣
\v 18 እባቦችን ይይዛሉ፣ የሚገድል ነገር እንኳን ቢጠጡ አይጎዳቸውም፣ እጆቻቸውን በህሙማን ላይ ይጭናሉ እነርሱም ይፈወሳሉ፡፡
\s5
\v 19 ጌታ ኢየሱስ ይህንን ካላቸው በኋላ ወደ ሰማይ ወጥቶም በእግዚአብሔር ቀኝ ተቀመጠ፡፡
\v 20 እነርሱም ወጥተው በየቦታው ሰበኩ፡፡ ጌታም ቃሉን ተከትለው በሚመጡ ምልክቶች እያጸና ከእነርሱ ጋር ይሠራ ነበር፡፡ አሜን፡፡