am_ulb/39-MAL.usfm

119 lines
14 KiB
Plaintext

\id MAL
\ide UTF-8
\h ትንቢተ ሚልክያስ
\toc1 ትንቢተ ሚልክያስ
\toc2 ትንቢተ ሚልክያስ
\toc3 mal
\mt ትንቢተ ሚልክያስ
\s5
\c 1
\p
\v 1 በሚልክያስ በኩል ወደ እስራኤል የመጣው የያህዌ ቃል ዐዋጅ ይህ ነው።
\v 2 “እኔ ወድጃችኋለሁ” ይላል ያህዌ። እናንተ ግን፣ “እንዴት ወደድኸን?” ብላችኋል? “ዔሳው የያዕቆብ ወንድም አልነበረምን? ያዕቆብን ወደድሁ
\v 3 ዔሳውን ግን ጠላሁ። ተራራውን ባድማ አደረግሁ፤ ርስቱንም የምድረ በዳ ቀበሮዎች መኖሪያ አደረግሁ።”
\s5
\v 4 ኤዶምያስ፣ “ብንደመሰስ እንኳ፣ የፈረሰውን መልስን እንሠራዋለን” ይል ይሆናል፤ የሰራዊት ጌታ ያህዌ እንዲህ ይላል፤ “እነርሱ የሠሩ ይሆናል፤ እኔ ግን መልሼ አፈርሳለሁ።” ሌሎች ሰዎች፣ “የዐመፀኞች አገር፤ ያህዌ ለዘላለም የተቆጣው ሕዝብ” በማለት የጠሯቸዋል።
\v 5 የገዛ ዓይኖቻችሁ ይህን ያያሉ። ከእስራኤል ዳርቻዎች ወዲያ እንኳ ያህዌ ትልቅ ነው ትላላችሁ”
\s5
\v 6 ለእናንተ ስሜን ለታቃልሉ ካህናት “ልጅ አባቱን ያከብራል፤ አገልጋይም ጌታውን ያከብራል። እኔ አባት ከሆንሁ፣ ታዲያ፣ ክብሬ የታለ? ጌታስ ከሆንሁ፣ መፈራቴ የታለ? ይላል የሰራዊት ጌታ ያህዌ። እናንተ ግን፣ “ስምህን ያቃለልነው በመንድነው?” ብላችኋል።
\v 7 መሠዊያዬ ላይ የረከሰ ምግብ በማቅረብ ነው። እናንተ፣ “ያረከስንህ በምንድነው” ብላችኋል። የእግዚአብሔር ገበታ የተናቀ ነው በማለታችሁ ነው።
\s5
\v 8 የታወረውን እንስሳ መሥዋዕት ማቅረብ፣ በደል አይደለም? አንካሳውንና በሽተኛውን መሥዋዕት ማቅረብስ በደል አይደለም? እስቲ ያንኑ ለባለሥልጣን አቅርቡት፣ ይቀበላችኋልን? ወይስ በእናንተ ደስ ይለዋልን?” ይላል የሰራዊት ጌታ ያህዌ።
\v 9 አሁን ግን እንዲራራልን የእግዚአብሔርን ፊት ፈልጉ። ለመሆኑ፣ እንዲህ ዓይነቱን መሥዋዕት ይዛችሁ ስትቀርቡ እርሱ ይቀበላችኋልን? ይላል የሰራዊት ጌታ ያህዌ።
\s5
\v 10 መሠዊያዬ ላይ ከንቱ እሳት እንዳታነዱ፣ ምነው ከእናንተ አንዱ የቤተመቅደሱን ደጆች በዘጋ ኖሮ! በእናንተ ደስ አልሰኝም፤ ከእጃችሁም ማንኛውንም መሥዋዕት አልቀበልም ይላል የሠራዊት ጌታ ያህዌ።
\v 11 ከፀሐይ መውጫ ጀምሮ እስከ መግቢያው ድረስ በሕዝቦች መካከል ስሜ ታላው ይሆናል፤ በየቦታው ሁሉ በስሜ ዕጣንና ንጹሕ መሥዋዕት ይቀርባል። በሕዝቦች መካከል ስሜ ታላቅ ይሆናል” የሠራዊት ጌታ ያህዌ።
\v 12 እናንተ ግን “የእግዚአብሔር ማዕድ የረከሰ ነው በማለት ታረክሱታላችሁ፤ ምግቡም የተናቀ ነው” በማለት ታቃልሉታላችሁ።
\s5
\v 13 ደግሞም፣ “ይህ ድካም ነው” በማለት ፣ “በንቀት ጢቅ አላችሁበት” ይላል የሠራዊት ጌታ ያህዌ። በዱር እንስሳ ተወስዶ የነበረውን ወይም አንካሳና በሽተኛውን መሥዋዕት ለማቅረብ ታመጣላችሁ። ታዲያ፣ ይህን ከእናንተ እጅ ልቀበል?” ይላል ያህዌ።
\v 14 “መንጋው ውስጥ ያለውን ተባዕት በግ መሥዋዕት ለማቅረብ ተስሎ ሳለ ለእኔ ነውር ያለበትን እንስሳ የሚያቀርብ አታላይ ርጉም ይሁን! እኔ’ኮ ታላቅ ንጉሥ ነኝ፤ ስሜም በአሕዛብ መካከል ይከበራል” ይላል የሠራዊት ጌታ ያህዌ።
\s5
\c 2
\p
\v 1 አሁንም፣ እናንተ ካህናት ይህ ትእዛዝ ለእናንተ ነው።
\v 2 “የማትሰሙና ለስሜ ክብር ለመስጠት በልባችሁም የማታኖኑት ከሆነ” ይላል የሠራዊት ጌታ ያህዌ፣ “መርገም እልክባችኋለሁ፤ በረከታችሁን እረግማለሁ። ትእዛዜን በልባችሁ አላኖራችሁምና በእርግጥ ረግሜአችኋለሁ።
\s5
\v 3 ዘራችሁን እገሥጻለሁ፤ የመሥዋዕታችሁንም ፋንድያ ፊታችሁ ላይ እበትናለሁ፤ እናንተም ከእርሱ ጋር ትጠፋላችሁ።
\v 4 ኪዳኔ ከሌዊ ጋር ይሆን ዘንድ ይህን ያዘዝሁ እኔ መሆኔንም ታውቃላችሁ” ይላል የሠራዊት ጌታ ያህዌ።
\s5
\v 5 “ከእርሱ ጋር ያደረግሁት ኪዳን የሕይወትና የሰላም ኪዳን ነበር፤ እነዚህን ለእርሱ ሰጠሁት፤ አከበርኩት፤ እርሱ አከበረኝ፤ በስሜ ፊት በፍርሃት በመንቀጥቀጥ ቆመ።
\v 6 እውነተኛ ትምህርት በአንደበቱ ነበር፤ በከንፈሮቹ ምንም ሐሰት አልተገኘም። በሰላምና በጽድቅ ከእኔ ጋር ተመላለሰ፤ ብዙዎችንም ከኅጢአት መለሰ።
\v 7 የካህኑ ከንፈሮች ዕውቀትን ይጠብቃሉ፤ እርሱ የሠራዊት ጌታ የያህዌ መልዕክተኛ ስለሆነ ሰዎች ከአፉ ትምህርት መፈለግ ይኖርባቸዋል።
\s5
\v 8 እናንተ ግን ከእውነተኛው መንገድ ወጥታችኋል። ሕጉን በተመለከተም ብዙዎችን አሰናክላችኋል፤ የሌዊን ኪዳን አፍርሳችኋል።” ይላል የሠራዊት ጌታ ያህዌ።
\v 9 “መንገዴን አልጠበቃችሁም፤ ትምሕርቱን በተመለከተ አድልዎ አድርጋችኋል፤ ስለዚህ እኔም በሰዎች ሁሉ ፊት እንድትዋረዱና እንድትናቁ አደርጋለሁ።”
\s5
\v 10 ለሁላችንም ያለን አንድ አባት አይደለምን? የፈጠረንስ አንድ አምላክ አይደለምን? ታዲያ፣ እያንዳንዱ ሰው ለወንድሙ ታማኝ ባለመሆን የአባቶቻችንን ኪዳን ያረከስነው ለምንድንው?
\v 11 ይሁዳ አልታመነም። በእስራኤልና በኢየሩሳሌም አስጸያፊ ነገር ተፈጽሞአል።
\v 12 እንዲህ የሚያደርገውን ሰው፣ ሌላው ቀርቶ ለሠራዊት ጌታ ለያህዌ መሥዋዕት የሚያመጣ እንኳ ቢሆን፣ ያህዌ ከያዕቆብ ድንኳኖች ያስወግደው።
\s5
\v 13 እናንተ ይህንንም አድርጋችኋል፣ የያህዌን መሠዊያ በእንባ አጥለቅልቃችኋል፤ እርሱ ቁርባናችሁን ስለማይመለከት ወይ በደስታ ከእጃችሁ ስለማይቀበለው ትጮኻላችሁ ታለቅሳላችሁም።
\s5
\v 14 እናንተም፣ “ይህ ለምን ሆነ?” በማለት ትጠይቃላችሁ። እንዲህ የሆነው ያህዌ በአንተና በወጣትነት ሚስትህ መካከል ምስክር ስለሆነ ነው፤ የቃል ኪዳን ጓደኝህና ሚስትህ ብትሆን እንኳ አንተ ለእርሷ ታማኝ አልነበርክም።
\v 15 በመንፈሱ ክፋይ እግዚአብሔር አንድ አላደረጋቸውምን? እርሱ አንድ ያደረጋችሁ ለመንድነው? ምክንያቱም ለእግዚአብሔር የሚሆን መሥዋዕት ስለፈለገ ነው። ስለዚህ በመንፈሳችሁ ራሳችሁን ጠብቁ፤ ከወጣትነት ሚስታችሁ ጋር ያላችሁንም ታማኝነት አታጉድሉ።
\v 16 “እኔ መፋታትን እጠላለሁ” ይላል የእስራኤል አምላክ ያህዌ፤ “ልብሱን በግፍ ሥራ የሚሸፍነውንውም ሰው እጠላለሁ” ይላል የሠራዊት ጌታ ያህዌ። “ስለዚህ በመንፈሳችሁ ራሳችሁን ጠብቁ፤ ታማኝነታችሁንም አታጉድሉ።”
\s5
\v 17 በቃላችሁ ያህዌን አታክታችኋል። እናንተ ግን፣ “እርሱን ያታከትነው በምንድነው?” ብላችኋል። “ክፉ የሚያደርግ ሁሉ በያህዌ ፊት መልካም ነው፤ እርሱም በክፉዎች ደስ ይለዋል፤ ወይም፣ “የፍትህ አምላክ ወዴት ነው?” በመለታችሁ ነው።
\s5
\c 3
\p
\v 1 “እነሆ፣ መልእክተኝዬን እልካለሁ፤ እርሱም መንገዴን በፊቴ ያዘጋጃል። እናንተ የምትፈልጉትም ጌታ በድንገት ወደ መቅደሱ የመጣል። ደስ የምትሰኙበትን የቃል ኪዳኑ መልእክተፍኛ ለመጣ ነው” ይላል የሠራዊት ጌታ ያህዌ።
\v 2 እርሱ የሚመጠበትን ቀን ማን መቋቋም ይችላል? እርሱ ሲገለጥ ማን ፊቱ መቆም ይችላል? ምክናቱም እርሱ እንደ አንጥረኛ እሳት፣ እንደ ለብስ አጠቢ ሳሙና ነው።
\v 3 ብር እንደሚያጠራና እንደ እንደሚያነጻ ሰው ይቀመጣል፤ የሌዊንም ልጆች ያጠራል እንደወርቅና እንደብር ያጠራቸዋል፤ እነርሱም የጽድቅን ቁርባን ለያህዌ ያመጣሉ።
\s5
\v 4 ያኔ የይሁዳና የኢየሩሳሌም ቁርባን እንደ ቀድሞ ዘመን፣ እንደጥንቱም ዘመን ያህዌን ደስ ያሰኘዋል።
\v 5 “በዚያ ጊዜ እኔ ለፍርድ ወደ እናንተ እቀርባለሁ። በመተተኞችና በአመንዝራዎች ላይ፣ በሐሰተኛ ምስክሮችና የሠራተኞቻቸውን ደመወዝ በሚከለክሉ ላይ፣ መበለቶችንና ድኻ አደጉን በሚጨቁን ላይ፣ መጻተኞችን ፍትሕ በሚነፍጉ ላይ፣ እኔንም በማያከብሩ ላይ በፍጥነት እመሰክርባቸዋለሁ” ይላል የሠራዊት ጌታ ያህዌ።
\s5
\v 6 እኔ ያህዌ አልተለወጥሁም፤ ስለዚህ እናንተ የያዕቆብ ልጆች አልጠፋችሁም።
\v 7 ከአባቶቻችሁ ዘመን ጀምሮ ከትእዛዞቼ ፈቀቅ ብላችኋል፤ እነርሱንም አልጠበቃችሁም። ወደ እኔ ተመለሱ፤ እኔም ወደ እናንተ እመለሳለሁ ይላል የሠራዊት ጌታ ያህዌ። እናንተ ግን፣ “የምንመለሰው እንዴት ነው?” ብላችኋል።
\s5
\v 8 ሰው ከእግዚአብሔር ይሰርቃልን? እናንተ ግን ከእኔ ሰርቃችኋል፤ ያም ሆኖ ግን፣ “ከአንተ የሰረቅነው እንዴት ነው?” ብላችኋል። በዐሥራትና በበኩራት ነው።
\v 9 እናንተም ሆናችሁ መላው ሕዝብ ከእኔ ሰርቃችኋልና የተረገማችሁ ናችሁ።
\s5
\v 10 በቤቴ መብል እንዲኖር ሙሉ አስራት ወደጎተራ አስገቡ። “በቂ ቦታ እስከማይኖራችሁ ድረስ የሰማይን መስኮት ከፍቼ በረከትን ባላፈስስላችሁ በዚህ አሁን ፈትኑኝ” ይላል የሠራዊት ጌታ ያህዌ።
\v 11 የምድራችሁን ፍሬ እንዳያጠፋ እህላችሁን የሚያጠፉትን እገሥጻለሁ። እርሻ ላይ ያለው የወይን ተክላችሁም ፍሬ አልባ አይሆንም” ይላል የሠራዊት ጌታ ያህዌ።
\v 12 የምድር ደስታ ስለምትሆኑ ሕዝቦች ሁሉ ቡሩካን ብለው ይጠሯችኋል” ይላል የሠራዊት ጌታ ያህዌ።
\s5
\v 13 “እኔ ላይ የድፍረት ቃል ተናግራችኋል” ይላል ያህዌ። እናንተ ግን፣ “በአንተ ላይ የተናገርነው ምንድነው?” ትላላችሁ።
\v 14 “እግዚአብሔርን ማገልገል ከንቱ ነው ብላችኋል። የእርሱን ትእዛዞች መጠበቅ፣ ወይም በሠራዊት ጌታ በያህዌ ፊት ሐዘንተኞች ሆነን መመላለሳችን ጥቅሙ ምንድነው?” ብላችኋል።
\v 15 ስለዚህም አሁን እብሪተኞችን ቡሩካን እንላቸዋለን። ክፉ አድራጊዎችን መበልጸግ ብቻ ሳይሆን፣ እግዚአብሔርን የሚፈታተኑትም ያመልጣሉ።
\s5
\v 16 ከዚያም ያህዌን የሚፈሩ እርስ በርሳቸው ተነጋገሩ። እግዚአብሔርም ሰማ፤ አደመጠም፤ ያህዌን ስለሚፈሩትና ስሙንም ስለሚያከብሩት ሰዎች በፊቱ መታሰቢያ እንዲሆን ተጻፈ።
\s5
\v 17 “እነርሱ የእኔ ይሆናሉ” ይላል የሠራዊት ጌታ ያህዌ፣ “እኔ በምሠራበት ቀን ርስቴ ይሆናሉ። ለሚያገለግለው ልጁ እንደሚራራ ሰው እኔም እራራላቸዋለሁ።
\v 18 በጻድቁና በዐመፀኛው መካከል፣ እግዚአብሔርን በሚያመልኩና እርሱን በማያመልኩ መካከል እንደገና ትለያላችሁ።
\s5
\c 4
\p
\v 1 “እብሪተኞችና ክፉ አድራጊዎች በሙሉ ገለባ የሚሆኑበት እንደምድጃ እሳት የሚነድ ቀን ይመጣል። የሚመጣው ቀን ያነዳቸዋል” ይላል የሠራዊት ጌታ ያህዌ፤ “ሥርም ሆን ቅርንጫፍ አይተውላቸውም።
\v 2 ስሜን ለምትፈሩ ለእናንተ ግን ፈውስ በክንፎቹ የያዘ የጽድቅ ፀሐይ ይወጣላቸዋል። እናንተም ከጋጥ እንደተለቀቁ እንቦሳ እየቦረቃችሁ ትወጣላችሁ።
\v 3 እኔ በምሠራበት ቀን ዐመፀኛውን ትረግጣላችሁ፤ ከእግራችሁ ጫማ በታች ዐመድ ይሆናሉ” ይላል የሠራዊት ጌታ ያህዌ።
\s5
\v 4 ለእስራኤል ሁሉ ሕጎችና ሥርዐቶች ይሆኑ ዘንድ ለአገልጋዬ ለሙሴ በኮሬብ የሰጠሁትን ትምህርቶች አስታውሱ።
\v 5 ታላቁና አስፈሪው የያህዌ ቀን ከመምጣቱ በፊት ነቢዩ ኤልያስን እልክላችኋለሁ።
\v 6 መጥቼ ምድርን ፈጽሜ እንዳላጠፋ የአባቶችን ልብ ወደ ልጆች የልጆችንም ልብ ውደ አባቶች ይመልሳል።